ዕዙ ለሁለት ወራት ያሰለጠናቸዉን አመራሮች አስመረቀ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ለሁለት ወራት ያሰለጠናቸዉን የዕዙ እና የሪፐፕሊካን ጥበቃ ሃይል የሻምበል እና የሻለቃ አመራሮች ያስመረቀ ሲሆን በምረቃ ስነ-ስርዓቱም የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ በክብር እንግድነት ተገኝተዉ ለአመራሮቹ መልዕክትና የስራ መመሪያ አሥተላልፈዋል፡፡

አመራሮቹ ከአሁን በፊትም ሲመሩ የመጡ እና ግዳጃቸዉን በብቃት መፈፀም የቻሉ መሆናቸዉን ጠቅሰዉ አሁን ደግሞ በስልጠና ያገኙትን አቅም እና እዉቀት ደምረዉ ዉጤታማ ስራ ለመስራት የሚያስችል አቅም መፍጠራቸዉን ጠቅሰዋል፡፡

የነበሩትን ጠንካራ ጎኖች በማቀብ እና ክፍተቶችን በመሙላት እንዲሁም ግዳጅን በአጭር ጊዜ መፈፀም የሚያስችል ቁመና በመገንባት በተገቢዉ መንገድ መስራት ይጠበቅባችኋል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አመራሮች አና የሪፐፕሊካን አመራሮች በጋራ መሰልጠን አንዱ ለአንዱ ጋሻ እና ደጀን በመሆን ግዳጅን ለመፈፀም እንደሚያስችል የጠቀሱት ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ ቀይ ቦኔት ሁኔታ ቀያሪ እና ዲስፕሊን መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

የሰልጣኞችን የቆይታ ጊዜ በማስመልከት ለክብር እንግዳዉ የስላጠና ሪፖርት ያቀረቡት የአመራር ትምህርት ቤት አዛዡ ሌተናል ኮሎኔል ሰማሃኝ ሃይሉ የተሰጠዉ ትምህርት የአመራር ትምህርት መሆኑን በመጥቀስ ስልጠናውም የነበረዉን ክፍተት እንዲሞላ እና የመሪነት ሚናዉን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡

ተመራቂ አመራሮቹም የወሰዱት ስልጠና ጊዜዉን ያገናዘበ እና ጥሩ አቅም እና ግንዛቤ የጨበጡበት እንዲሁም በቀጣይ ግዳጅን በአጭር ጊዜ በላቀ ውጤት መፈፀም የሚያስችል የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ትምህርት እንደነበረ  በስልጠና ላይ የቆዩት ሻለቃ ሃብቱ ገብረኪዳን እና ሻለቃ ሽባበዉ ፈጫሳ ገልፀዋል፡፡

ዘጋቢ ምህረት ስመኝ
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ