ዕዙ ከየትኛውም አቅጣጫ ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን መመከት በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ ።
ዋና አዛዡ ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዕዙ የግዳጅ ቀጣናዎች አሁናዊ የተልዕኮ አፈፃፀም ዙሪያ የመስክ ምልከታና ቅኝት አድርገዋል።
ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከከፍተኛ አመራሮቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሠራዊቱ ዝግጁነትና ተልዕኮ አፈፃፀም የባዳውን ዕኩይ ሴራዎች መከታተልና መቆጣጠር በሚያስችል ደረጃ የተጠናከረ መሆኑን አንሰተዋል።

የባንዳዎቹ ተስፋ ከባዳዎቹ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባንዳዎቹ ህይወታቸውን ለማቆየት ከባዳዎቹ የሚጠብቁት ፍርፋሪና ባዳዎቹ በህገወጥ መንገድ ማግበስበስ የሚፈልጉት የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት በጠንከራ ቁጥጥርና ክትትል የበለጠ መጥበብ አለበት ሲሉም አሳስበዋል።
የሠራዊቱ አሰፋፈር፣ ቁርጠኝነትና የስነ-ልቦና ዝግጁነት ከመቼውም ጊዜ የላቀ ነው ያሉት ዋና አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባዳዎቹ ስለ ኢትዮጵያ ምንም ሊያስቡ ይችላሉ ነገር ግን ለመተንኮስ ሲያስቡ ከባድ ዋጋ እንደሚከፍሉም ጭምር ማሰብ ይገባቸዋልም ብለዋል።
በፅንፈኛው ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ በላኪውም ሆነ በተላላኪው ላይ ድንጋጤ ፈጥሯል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የሠላም አማራጭ በማይከተሉ፣የኢትዮጵያን ልማት በሚያደናቅፉና የባዳዎቹን ተልዕኮ ለማስፈፀም በሚፍጨረጨሩ ኃይሎች ላይ የምንወስደው እርምጃ ጠንከር ያለ ነው ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዘገባው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official





