ሚኒስትሮች የመከላከያ ሪፈራል ሆስፒታልን የንፅህና አስተዳደር ስርዓት ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ጎበኙ

የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ   በቢሸፍቱ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል በመገኘት የንፅህና አስተዳደር ስርዓቱን ስታንዳርድ ለመጠበቅ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ጎብኝተዋል፡፡

ሚኒስትሮቹ የሆስፒታሉን የንፅህና ስርዓት አቅም ለማዘመንና ለማስፋት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በአንድ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የሆስፒታሉን የላውንደሪና የሃይጂን ስርዓቱን በማዘመን ተግባራዊ ስልጠና በመስጠት ስራውን ለማሳለጥ የተደረገውን ጥረትም ተመልክተዋል፡፡

ይህ ጥረት የሆስፒታሉን አጠቃላይ የመገልገያ አልባሳት፣ የታካሚ ልብሶችንና ቁሳቁሶችን እንዲሁም ሙሉ የንፅህ አጠባበቅ ሂደቱን ዘመናዊና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በማጣጣም የደህንነት መስፈርቶችን እንዲያሟላ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

ፖሽ የላውንደሪና የሃይጂን ሶሉሽን በተሰኘው ድርጅት ድጋፍ የተከናወነው ይህ ዘመናዊ የንፅህና ስርዓት አተገባበር ሆስፒታሉ ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥና የኢንፌክሽን መከላከል አቅሙን ይበልጥ የሚያሻሽል መሆኑም የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ  ለሆስፒታል ባለሙያዎች ተከታታይና ተግባራዊ ስልጠና በመስጠት ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ከማድረጉም  በላይ የሰራተኞች የፅዳት ዩኒፎርሞችን፣ደረጃቸውን የጠበቁ የላውንደሪ ኬሚካሎችንና አንሶላዎች ድጋፍ ማድረጉም ተመልክቷል፡፡

ሚኒስትሮቹ የድርጅቱ ባለቤት አቶ መሃመድ ቡሽራ ለሆስፒታሉ ያበረከቱት ድጋፍ  የሚደነቅ መሆኑን በመግለፅ ዕውቅናና ምስጋና ሰጥተዋቸዋል፡፡

የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል በኢትዮጵያ ውስጥ ልዩ የህክምና አገልግሎቶችን በመስጠት ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ሲሆን አሁን የተዘረጋው ዘመናዊ የንፅህና አጠባበቅ ስርዓት የታካሚዎችን ደህንነት ይበልጥ በማሻሻል ከሀገር ውጭ የሚደረግ የህክምና ጉዞን በመቀነስ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በጉብኝቱ ላይ ጄኔራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያዎችና የሆስፒታሉ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡ ዘገባውን ያደረሠን የሚኒስቴሩ ፅህፈት ቤት ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ስፖርት

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ