የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ኀዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢትዮጵያና አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋትን ለማረጋገጥ በሚያስችላቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዘዥ ጄኔራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰን የተመራ ልዑክ ከኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋትን ለመፍጠር የቀጠናው ሐገራት በትብብር መሥራት እንዳለባቸውም ነው የተመላከተው።
ሁለት ሐገራት ወታደራዊን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ለበርካታ ዓመታት በትብብር እየሠሩ መምጣታቸውን ያነሱት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተች ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷ ለሠላማዊና ኢኮኖሚዋን ለመገንባት መሆኑን ያብራሩት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ከአሜሪካ ጋር ያለው ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ አልሸባብን ለማዳከምና የሽብር ሴራውን ለማክሸፍ የምትወስደውን የኃይል እርምጃ አጠናክራ ትቀጥላለች።
ኢትዮጵያ በቀጠናው ፀጥታን ለማስፈን እየተጫወተች ያለችውን ሚና ያደነቁት የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰን ሽብርተኝነትን በጋራ የመዋጋት ሥራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሠላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን መንገድ እንደሚደግፉ የገለፁት የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዡ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ብትወጣ የበለጠ ለቀጠናው ሠላም ትሠራለች ብለው እንደሚያምኑ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ በኩል ያሉ ፍላጎቶችንና በቀጠናው ሠላምን ለማረጋገጥ ስለያዘቻቸው ዕቅዶች ከዋሽንግተን ዲሲ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩም ጠቁመዋል።
በዕለቱ “የአፍሪካ ቀንድ የሠላም ሁኔታ” በሚል ርዕስ በኮሎኔል መስፍን አውላቸው ጥናታዊ ፅሑፍ ቀርቦ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሁለቱ ሐገራት ስጦታ ተሰጣጥተዋል።
ዘጋቢ ውብሸት አንበሴ
ፎቶግራፍ አበረ አየነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official