ስነ ልቦና የሠራዊቱን ሞራላዊ ልዕልና በመገንባት አስቻይ አቅም መሆኑ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የስነ ልቦና ስራ ጥልቅ ሀገራዊ ስሜት በመፍጠር ተልዕኮዎችን በከፍተኛ ተነሳሽነት እና ውጤታማነት ለመፈፀም የሚያስችል ሞራላዊ ልዕልናን የሚያስታጥቅ ትልቅ አቅም መሆኑን የማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሜጄር ጄኔራል ሙላት ጀልዱ ገለፁ።
ጄኔራል መኮንኑ ይህንን የተናገሩት የዕዙ የሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ የበጀት አመት የሥራ ማጠቃለያ በመገኘት ለክፍሉ ውጤታማ አፈፃፀም ጉልህ ድርሻ የነበራቸውን የስታፍ ክፍሎች፣ ተቋማትን በማመስገን የክፍሉን አባላት ባበረታታበት በክብር እንግድነት በተገኙበት መድረክ ነው።
የማዕከላዊ ዕዝ ስነ ልቦና ሰራዊቱ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና በመገኘት ማንኛውንም መስዋዕትነት እየከፈለ የሰራዊቱን ስነ ልቦናዊ ዝግጁነት በኪነታዊ ልባስ የገነባ አይነተኛ መሳሪያ ነው ያሉት ሜጄር ጀኔራል ሙላት ጀልዱ ጀግንነትን ፣ የሀገር እና የአሀድ ፍቅርን በሰራዊቱ የልቦና ውቅር እየዘራ የመጣ ክፍል ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ዕዝ የሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ በስሩ የሚገኙ ቡድኖችን በመጠቀም ወቅቱ የሚጠይቀውን የሰራዊት ግንባታ ስትራቴጅዎችን የሚጠቀም ተልዕኮን ማዕከል ያደረገ የዲጅታላይዜሽን ስራ ተግባራዊ እያደረገ የመጣ መሆኑን ያነሱት የዕዙ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ሀላፊ ኮሎኔል ለችሳ መገርሳ ናቸው።
የጅማ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ፈቀደ ታመነ በበኩላቸው ማዕከላዊ ዕዝ ከጅማ ዞን መስተዳዲርና ህዝብ የሰላምና የፀጥታ ስራዎችን በጋራ በመስራት አስተማማኝ ሰላም ማምጣት የቻለ የምንኮራበት ዕዝ ነው ብለዋል።
የዕዙ የሰራዊት ስነ ልቦና ግምባታ ደግሞ ብሔራዊ ባዕላትን እንድሁም ሌሎች ህዝባዊ መድረኮችን እየተጠቀመ በጥበባዊ ለዛ ሰራዊቱንና ህብረተሰቡን ይበልጥ ያቀራረበ ክፍል መሆኑን ሀላፊው ገልፀዋል።
በዕለቱ የማዕከላዊ ዕዝ ስታፍ አመራርና አባላት ፣ የጅማ ዞን የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የዩንቨርስቲ አመራሮች ፣ አጋር የፀጥታ አካላት እና የሀይማኖት አባቶች የተገኙ ሲሆን የተለያዩ ኪነታዊ ዝግጅቶች ለታዳሚው ቀርበዋል።
ዘጋቢ መሀመድ አህመድ
ፎቶግራፍ ሚኪያስ እስክንድር
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የስነ ልቦና ስራ ጥልቅ ሀገራዊ ስሜት በመፍጠር ተልዕኮዎችን በከፍተኛ ተነሳሽነት እና ውጤታማነት ለመፈፀም የሚያስችል ሞራላዊ ልዕልናን የሚያስታጥቅ ትልቅ አቅም መሆኑን የማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሜጄር ጄኔራል ሙላት ጀልዱ ገለፁ።
ጄኔራል መኮንኑ ይህንን የተናገሩት የዕዙ የሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ የበጀት አመት የሥራ ማጠቃለያ በመገኘት ለክፍሉ ውጤታማ አፈፃፀም ጉልህ ድርሻ የነበራቸውን የስታፍ ክፍሎች፣ ተቋማትን በማመስገን የክፍሉን አባላት ባበረታታበት በክብር እንግድነት በተገኙበት መድረክ ነው።
የማዕከላዊ ዕዝ ስነ ልቦና ሰራዊቱ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና በመገኘት ማንኛውንም መስዋዕትነት እየከፈለ የሰራዊቱን ስነ ልቦናዊ ዝግጁነት በኪነታዊ ልባስ የገነባ አይነተኛ መሳሪያ ነው ያሉት ሜጄር ጀኔራል ሙላት ጀልዱ ጀግንነትን ፣ የሀገር እና የአሀድ ፍቅርን በሰራዊቱ የልቦና ውቅር እየዘራ የመጣ ክፍል ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ዕዝ የሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ በስሩ የሚገኙ ቡድኖችን በመጠቀም ወቅቱ የሚጠይቀውን የሰራዊት ግንባታ ስትራቴጅዎችን የሚጠቀም ተልዕኮን ማዕከል ያደረገ የዲጅታላይዜሽን ስራ ተግባራዊ እያደረገ የመጣ መሆኑን ያነሱት የዕዙ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ሀላፊ ኮሎኔል ለችሳ መገርሳ ናቸው።
የጅማ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ፈቀደ ታመነ በበኩላቸው ማዕከላዊ ዕዝ ከጅማ ዞን መስተዳዲርና ህዝብ የሰላምና የፀጥታ ስራዎችን በጋራ በመስራት አስተማማኝ ሰላም ማምጣት የቻለ የምንኮራበት ዕዝ ነው ብለዋል።
የዕዙ የሰራዊት ስነ ልቦና ግምባታ ደግሞ ብሔራዊ ባዕላትን እንድሁም ሌሎች ህዝባዊ መድረኮችን እየተጠቀመ በጥበባዊ ለዛ ሰራዊቱንና ህብረተሰቡን ይበልጥ ያቀራረበ ክፍል መሆኑን ሀላፊው ገልፀዋል።
በዕለቱ የማዕከላዊ ዕዝ ስታፍ አመራርና አባላት ፣ የጅማ ዞን የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የዩንቨርስቲ አመራሮች ፣ አጋር የፀጥታ አካላት እና የሀይማኖት አባቶች የተገኙ ሲሆን የተለያዩ ኪነታዊ ዝግጅቶች ለታዳሚው ቀርበዋል።
ዘጋቢ መሀመድ አህመድ
ፎቶግራፍ ሚኪያስ እስክንድር
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
Telegram
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
👍13❤8
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ስር እየተካሄዱ ያሉ የአዳማ ጋርመንትና ኢንዱስትሪ፣ የጋሻ የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት እና የመከላከያ ባጅና ሜዳሊያ ማምረቻ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ያስገነባውን አዲስ የማስፋፊያና የማሻሻያ ፕሮጀክት በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
በጋሻ መኖሪያ ፕሮጀክት፣ በአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ እንዲሁም በመከላከያ ባጅና ሜዳሊያ ማምረቻ ፋብሪካ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን የጎበኙት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የፋውንዴሽኑን አመራሮችና ሰራተኞች ላስመዘገቡት ውጤት አመስግነው፣ የተገኘው ለውጥ ሳያዘናጋቸው ለበለጠ ውጤት እንዲተጉ አሳስበዋል።
በቀጣይም የምርት ጥራትን በማሻሻል፣ የምርምርና የቴክኖሎጂ ልማትን በማስፋፋት፣ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን በማጠናከር፣ የግብዓት አቅርቦትን በራስ አቅም በማሳደግ በአፍሪካ ደረጃ ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪ እንዲገነባ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
"ሰራዊቱ መለኪያው ሀገሩ ነው" ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን የተቋሙንና የሀገሪቱን ፍላጎት በማሳካት ያለውን ሚና ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባው አመላክተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሀይሉ ጀልዱን ጨምሮ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና የፋውንዴሽኑ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ስር እየተካሄዱ ያሉ የአዳማ ጋርመንትና ኢንዱስትሪ፣ የጋሻ የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት እና የመከላከያ ባጅና ሜዳሊያ ማምረቻ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ያስገነባውን አዲስ የማስፋፊያና የማሻሻያ ፕሮጀክት በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
በጋሻ መኖሪያ ፕሮጀክት፣ በአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ እንዲሁም በመከላከያ ባጅና ሜዳሊያ ማምረቻ ፋብሪካ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን የጎበኙት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የፋውንዴሽኑን አመራሮችና ሰራተኞች ላስመዘገቡት ውጤት አመስግነው፣ የተገኘው ለውጥ ሳያዘናጋቸው ለበለጠ ውጤት እንዲተጉ አሳስበዋል።
በቀጣይም የምርት ጥራትን በማሻሻል፣ የምርምርና የቴክኖሎጂ ልማትን በማስፋፋት፣ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን በማጠናከር፣ የግብዓት አቅርቦትን በራስ አቅም በማሳደግ በአፍሪካ ደረጃ ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪ እንዲገነባ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
"ሰራዊቱ መለኪያው ሀገሩ ነው" ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን የተቋሙንና የሀገሪቱን ፍላጎት በማሳካት ያለውን ሚና ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባው አመላክተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሀይሉ ጀልዱን ጨምሮ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና የፋውንዴሽኑ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
Telegram
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤19👍8
ቅንጅታዊ ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል ለውጤት እንደሚያበቃ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመከላከያ ፋውንዴሽን ስር በሚገኙ ተቋማት ያደረጉት የስራ ጉብኝትና የሰጡት አቅጣጫ በድርጅቶቹ ውስጥ ከፍተኛ ተነሳሽነት በመፍጠር ለቀጣይ የስራ አፈፃፀም ጠንካራ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሻ መሆኑን የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ የስራ ኃላፊዎች ተናገሩ።
የቴክስታይልና ጋርመንት ዘርፍ ኃላፊ ኮሎኔል አበበ አጥናፉ ፣ የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ኢንጅነር ደሱ አብዲሳ እና ምክትል ሥራ አስኪያጅ መቶ አለቃ ሁንዱማ ደሬሳ፣ ከ40 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለውን ተቋም ከነበረበት መቀዛቀዝ በማውጣት ወደ ትርፋማነት ለማሸጋገር የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ያደረጉት ያልተቋረጠ ክትትል፣ የሰጡት ድጋፍና የአመራር አቅጣጫ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
እንደ ሀላፊዎቹ ገለፃ፣ ፋብሪካው ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ዩኒፎርሞችና ሌሎች ቁሳቁሶችን ከማምረት ባለፈ፣ ለፌዴራልና ለክልል የፀጥታ ተቋማት እንዲሁም ለጎረቤት ሀገራት የጋርመንት ምርቶችን በማቅረብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተና አቅሙንም እያጠናከረ ይገኛል።
በተቋሙ የሰራተኞችን አቅም ለማጎልበት ተከታታይ ስልጠናዎች መሰጠታቸው፣ ሥራን በእውቀት፣ በተጠያቂነትና በባለቤትነት ስሜት መፈፀማቸው ለውጤታማነታቸው መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል።
ለማህበረሰቡ የሚሆኑ የጋርመንት ምርቶችን በተለያዩ የስርጭት አማራጮች ተደራሽ ለማድረግ እየሠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሀላፊዎቹ የ2019 የበጀት ዓመት ዕቅዶቻቸውን ከግብ ለማድረስና የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት እየሠሩ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከ40 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ በአምስት ፋብሪካዎች አማካኝነት ወታደራዊ ዩኒፎርሞችንና ሌሎች አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን፣ ከሁለት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድልም ፈጥሯል።
በመከላከያ ፋውንዴሽን ስር የሚገኘው የጋሻ የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት ለመከላከያ ሠራዊት አባላት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የጋራ የመኖሪያ ቤቶችን በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች እየገነባ ሲሆን፣ የመከላከያ ባጅና ሜዳልያ ማምረቻ ድርጅትም ለሠራዊቱና ለሌሎች ተቋማት ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን በማምረት ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመከላከያ ፋውንዴሽን ስር በሚገኙ ተቋማት ያደረጉት የስራ ጉብኝትና የሰጡት አቅጣጫ በድርጅቶቹ ውስጥ ከፍተኛ ተነሳሽነት በመፍጠር ለቀጣይ የስራ አፈፃፀም ጠንካራ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሻ መሆኑን የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ የስራ ኃላፊዎች ተናገሩ።
የቴክስታይልና ጋርመንት ዘርፍ ኃላፊ ኮሎኔል አበበ አጥናፉ ፣ የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ኢንጅነር ደሱ አብዲሳ እና ምክትል ሥራ አስኪያጅ መቶ አለቃ ሁንዱማ ደሬሳ፣ ከ40 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለውን ተቋም ከነበረበት መቀዛቀዝ በማውጣት ወደ ትርፋማነት ለማሸጋገር የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ያደረጉት ያልተቋረጠ ክትትል፣ የሰጡት ድጋፍና የአመራር አቅጣጫ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
እንደ ሀላፊዎቹ ገለፃ፣ ፋብሪካው ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ዩኒፎርሞችና ሌሎች ቁሳቁሶችን ከማምረት ባለፈ፣ ለፌዴራልና ለክልል የፀጥታ ተቋማት እንዲሁም ለጎረቤት ሀገራት የጋርመንት ምርቶችን በማቅረብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተና አቅሙንም እያጠናከረ ይገኛል።
በተቋሙ የሰራተኞችን አቅም ለማጎልበት ተከታታይ ስልጠናዎች መሰጠታቸው፣ ሥራን በእውቀት፣ በተጠያቂነትና በባለቤትነት ስሜት መፈፀማቸው ለውጤታማነታቸው መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል።
ለማህበረሰቡ የሚሆኑ የጋርመንት ምርቶችን በተለያዩ የስርጭት አማራጮች ተደራሽ ለማድረግ እየሠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሀላፊዎቹ የ2019 የበጀት ዓመት ዕቅዶቻቸውን ከግብ ለማድረስና የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት እየሠሩ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከ40 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ በአምስት ፋብሪካዎች አማካኝነት ወታደራዊ ዩኒፎርሞችንና ሌሎች አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን፣ ከሁለት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድልም ፈጥሯል።
በመከላከያ ፋውንዴሽን ስር የሚገኘው የጋሻ የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት ለመከላከያ ሠራዊት አባላት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የጋራ የመኖሪያ ቤቶችን በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች እየገነባ ሲሆን፣ የመከላከያ ባጅና ሜዳልያ ማምረቻ ድርጅትም ለሠራዊቱና ለሌሎች ተቋማት ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን በማምረት ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
Telegram
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤22👍4🔥2
አዳኝ ነብሮች ፦ ክፍል አንድ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የንጋት ዝግጁነት
"በበረሃዋ ንግሥት"፣ የፍቅር ከተማ በሆነችው ድሬደዋ፤ ፀሐይ ገና ከአድማስ ሳትወጣ ምድር በንጋት ድባብ ትደምቃለች።
በአንድ የጦር ካምፕ ውስጥ ግን ንጋት የአዲስ ቀን ጅማሮ ብቻ አይደለም፤ የአዲስ ተልዕኮ ጅማሮ ነው።
ከወፎች ዝማሬ በስተቀር አየሩ ፀጥ ያለ ቢመስልም፣ በዚያ ፀጥታ ውስጥ የማይታይ እንቅስቃሴ አስቀድሞ ተጀምሯል።
በኢትዮጵያ አየር ኃይል 3ኛው አየር ምድብ፣ 21ኛው ተዋጊ ሄሊኮፕተር ክንፍ፣ በብዙዎች "አዳኝ ነብሮች" ተብሎ በሚታወቀው ክንፍ፣ ሰዓት በጊዜ አይለካም፤ በተልዕኮ ይለካል።
ከመጀመሪያው የፀሐይ ጨረር በፊት የሚነቃው ሄሊኮፕተሩ ሳይሆን፣ የሀገር ሰማይ ጠባቂዎቹ ናቸው። የበረራ ልብሳቸውን የለበሱ አብራሪዎችና ቴክኒሻኖች እንደ ንስር ነቅተው ለተልዕኳቸው ተዘጋጅተዋል።
አብራሪዎቹ የቀኑን ተልዕኮ በጥንቃቄ ይገመግማሉ፤ የአየር ሁኔታን፣ የበረራ መስመሮችን፣ የመገናኛ ሥርዓቶችን እና የደህንነት ሂደቶችን እስከ መጨረሻው ያረጋግጣሉ።
በሌላ በኩል፣ ቴክኒሻኖች በእጃቸው መፍቻ፣ በአዕምሯቸው እውቀት፣ በልባቸው ኃላፊነት ተሸክመው ወደ ሄሊኮፕተሮቹ ይቀርባሉ።
ለእነሱ እያንዳንዱ ቦልት፣ እያንዳንዱ ብሌድ፣ እያንዳንዱ አካል በመደበኛ አሰራር ብቻ አይፈተሽም፤ የአንድ በረራ ደህንነት በእነዚህ ዝርዝሮች ላይ እንደሚመሰረት ስለሚያውቁ፣ ሁሉም በከፍተኛ ጥንቃቄ ይፈተሻሉ።
እዚህ "ትንሽ ስህተት" የሚባል ቃል ቦታ የለውም። ትክክለኛነት ባህል ነው፤ ጥንቃቄ ደግሞ የዕለት ተዕለት አኗኗር።
የሞተር ድምፅ ገና አልተሰማም፤ ነገር ግን የተልዕኮው ልብ መምታት አስቀድሞ ጀምሯል።
እዚህ ሄሊኮፕተር መብረር የሚጀምረው ከሞተር ማስነሳት አይደለም፤ ከዲሲፕሊን፣ ከዝግጁነት እና ከቡድን መተማመን ነው።
የዚህ ክንፍ ጥንካሬ በሚበሩት ሄሊኮፕተሮች ብቻ አይለካም፤ ከእነሱ ጀርባ በአንድ ዓላማ የቆሙ፣ በሙያቸው የተካኑ ወታደር ባለሙያዎች በሚያሳዩት ቁርጠኝነት ይለካል።
ለ"አዳኝ ነብሮች" እያንዳንዱ ንጋት አዲስ የሥራ ቀን ብቻ አይደለም፤ ለኢትዮጵያ የገቡትን አደራ በየቀኑ እንደገና የሚያፀኑበት የቁርጠኝነት ቃል ኪዳን ነው።
በዮናስ ጌታቸው
ይቀጥላል......
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የንጋት ዝግጁነት
"በበረሃዋ ንግሥት"፣ የፍቅር ከተማ በሆነችው ድሬደዋ፤ ፀሐይ ገና ከአድማስ ሳትወጣ ምድር በንጋት ድባብ ትደምቃለች።
በአንድ የጦር ካምፕ ውስጥ ግን ንጋት የአዲስ ቀን ጅማሮ ብቻ አይደለም፤ የአዲስ ተልዕኮ ጅማሮ ነው።
ከወፎች ዝማሬ በስተቀር አየሩ ፀጥ ያለ ቢመስልም፣ በዚያ ፀጥታ ውስጥ የማይታይ እንቅስቃሴ አስቀድሞ ተጀምሯል።
በኢትዮጵያ አየር ኃይል 3ኛው አየር ምድብ፣ 21ኛው ተዋጊ ሄሊኮፕተር ክንፍ፣ በብዙዎች "አዳኝ ነብሮች" ተብሎ በሚታወቀው ክንፍ፣ ሰዓት በጊዜ አይለካም፤ በተልዕኮ ይለካል።
ከመጀመሪያው የፀሐይ ጨረር በፊት የሚነቃው ሄሊኮፕተሩ ሳይሆን፣ የሀገር ሰማይ ጠባቂዎቹ ናቸው። የበረራ ልብሳቸውን የለበሱ አብራሪዎችና ቴክኒሻኖች እንደ ንስር ነቅተው ለተልዕኳቸው ተዘጋጅተዋል።
አብራሪዎቹ የቀኑን ተልዕኮ በጥንቃቄ ይገመግማሉ፤ የአየር ሁኔታን፣ የበረራ መስመሮችን፣ የመገናኛ ሥርዓቶችን እና የደህንነት ሂደቶችን እስከ መጨረሻው ያረጋግጣሉ።
በሌላ በኩል፣ ቴክኒሻኖች በእጃቸው መፍቻ፣ በአዕምሯቸው እውቀት፣ በልባቸው ኃላፊነት ተሸክመው ወደ ሄሊኮፕተሮቹ ይቀርባሉ።
ለእነሱ እያንዳንዱ ቦልት፣ እያንዳንዱ ብሌድ፣ እያንዳንዱ አካል በመደበኛ አሰራር ብቻ አይፈተሽም፤ የአንድ በረራ ደህንነት በእነዚህ ዝርዝሮች ላይ እንደሚመሰረት ስለሚያውቁ፣ ሁሉም በከፍተኛ ጥንቃቄ ይፈተሻሉ።
እዚህ "ትንሽ ስህተት" የሚባል ቃል ቦታ የለውም። ትክክለኛነት ባህል ነው፤ ጥንቃቄ ደግሞ የዕለት ተዕለት አኗኗር።
የሞተር ድምፅ ገና አልተሰማም፤ ነገር ግን የተልዕኮው ልብ መምታት አስቀድሞ ጀምሯል።
እዚህ ሄሊኮፕተር መብረር የሚጀምረው ከሞተር ማስነሳት አይደለም፤ ከዲሲፕሊን፣ ከዝግጁነት እና ከቡድን መተማመን ነው።
የዚህ ክንፍ ጥንካሬ በሚበሩት ሄሊኮፕተሮች ብቻ አይለካም፤ ከእነሱ ጀርባ በአንድ ዓላማ የቆሙ፣ በሙያቸው የተካኑ ወታደር ባለሙያዎች በሚያሳዩት ቁርጠኝነት ይለካል።
ለ"አዳኝ ነብሮች" እያንዳንዱ ንጋት አዲስ የሥራ ቀን ብቻ አይደለም፤ ለኢትዮጵያ የገቡትን አደራ በየቀኑ እንደገና የሚያፀኑበት የቁርጠኝነት ቃል ኪዳን ነው።
በዮናስ ጌታቸው
ይቀጥላል......
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
Telegram
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤22👍9👏4🔥2😁1