ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ኢንስፔክተር ጄኔራልና የደቡባዊ ዞን ጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ባሬድ የተመራ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።

በ1955 ዓ.ም አካባቢ በይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያና ሞሮኮ ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት  በፓን አፍሪካዊ  መንፈስ እና ለአህጉራዊ አንድነት የጋራ ቁርጠኝነት የታየበት ወሳኝ ወቅት እንደነበር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አስታውሰዋል።

ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ እና በራባት የተካሄደው የከፍተኛ ደረጃ ወታደራዊ ልዑካን ምክክርም ሁለቱ ሀገሮች በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን እንዲፈትሹ እድል ፈጥሮላቸው እንደነበር ተገልጿል።

የሞሮኮ ሮያል ጦር ኃይል ኢንስፔክተር ጄኔራልና የደቡባዊ ዞን ጦር አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሞሐመድ ባሬድ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃነት ምልክት መሆኗንና ወታደራዊ ትብብሩም ለአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ለምናበረክተው አስተዋፅኦ የጎላ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የአፍሪካ ቀጠና የሚገኙ መሆናቸውን የገለፁት የመከላከያ ውጪ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ተሾመ ገመቹ በየቀጠናቸው ከሚያበረክቱት አስተዋፅኦ በተጨማሪ በጋራ ለአፍሪካ ሰላምና ደህንነት እንዴት በትብብር መስራት እንዳለባቸውና ምን ምን ጉዳዮች ላይ መተባበር እንዳለባቸውም ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከሞሮኮ ወታደራዊ ተቋማት በቴክኖሎጂ ሽግግር በሳይበር በአየር ኃይልና በባህር ኃይል  ኢትዮጵያ የምትወስደው ተሞክሮ እንዳለ የገለፁት ጄነራል መኮንኑ  ኢትዮጵያ አሁን ላይ በኢንዱስትሪ እያሳየችው ካለው እምርታ አንፃር ደግሞ እነሱም አብረውን እንደሚሰሩና መጪውን ሁኔታ ያገናዘበ ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ በቀጠናው በሚኖሩ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮችም አብሮ ለመስራት የሚያስችል ውይይት መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በውይይቱ ላይ የአየር ኃይል የባህር ኃይል የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊዎች  ተገኝተዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት በቀጣይ የመግባቢያ ስምምነት ይፈራረማሉም ብለዋል፡፡ ውይይቱን ተከትሎ የልዑካን ቡድኑ በሆሚቾ አሙኔሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪና በአየር ኃይል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትንም ጎብኝቷል፡፡

በአብዮት ዋሚ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ