ጠንካራና ለቆመለት ዓላማ ፅኑ የሆነ፣ ግዳጁን በድል የሚወጣ ሠራዊት ተፈጥሯል።

ሌተናል ጄኔራል መሃመድ ተሰማ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

ምስራቅ ዕዝ በገርባሳ ማሰልጠኛ ማዕከል ከሁሉም ኮሮችና ስታፍ ልዩ ልዩ ክፍሎች ለተውጣጡ ሙያተኞችን  እያስለጠነ ይገኛል።

እነዚህ ሰልጣኞች የተለያዩ የሙያ ስልጠና፧ የስነልቦና ፣ የአካል ብቃት እና አሀድን ለውጊያ ማዘጋጀት ፣ የተዘጋጀውን አሀድ መምራት አንዲሁም ሌሎች ክህሎቶችን በመማር ላይ ይገኛሉ።

በማስልጠኛ ማዕከሉ የተገኙት የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ ፣ ጠንካራና ለቆመለት ዓላማ ፅኑ የሆነ፣ ግዳጁን በድል የሚወጣ ሠራዊት መፈጠሩን ጠቅሰው ሠራዊቱ የአገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ፣ የኢትዮጵያን ዳር ድንበርና የህዝብን አንድነት በሀይል ለመናድ የሚሰነዘርን ጥቃት በመመከት የአገራችንን ሰላምና አንድነት የማረጋገጥ ተልዕኮውን በድል እየተወጣ የሚገኝ የድል ሠራዊት ነው ብለዋል።

ሰራዊታችን የአልሸባብን ሴራና ተንኮል በመገንዘብ የምስራቁን ቦርደር አካባቢ እየጠበቀ ያለ መሆኑንና በምስራቅ ሃረርጌና ምዕራብ ሃረርጌ አካባቢ የሸኔን ጥፋት እያመከነ ያለ እንዲሁም በአማራ ክልልም የፅንፈኛውን ሃይል አገር የማፈረስ ተልዕኮ በማክሸፍ ግዳጁን በአስተማማኝ እየተወጣ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ሰአት የሀገራችንን ሰላምና እድገት የማይፈልጉ የውጭና የሀገር ውስጥ ጠላቶች ስላሉብን እየተዋጋን ለትላላቅ ሀገራዊ ግዳጅ መዘጋጀት ስላለብን ስልጠና ላይ የሞትገኙ ሰልጣኝ ሙያተኞች አቅማችሁን ይበልጥ በማጎልበት ተጨማሪ አቅም መፍጠር ይኖርባችኋል ብለዋል።

ሰልጠኞች የተቋሙን ንብረት በጥንቃቄ በመያዝ እና ጠንካራ አሀድ በመገንባት እንዲሁም በግዳጅ ላይ አሃድን በብቃት በመምራት ድል ማስመዝገብ የሚያስችል ክህሎት መኖር አለበት ሲሉ አሳስበዋል።

ሠራዊቱ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ ያፀና የበለፀገች አገር፣ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱንና ሃገረ መንግስቱን በመጠበቅ የአገሪቱን ብሔራዊ ክብር ያረጋገጠና መስዋዕትነትን በመክፈል የአገሪቱ የመጨረሻው ምሽግ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የሰለጠነና የተማረ የሰዉ ሃይል በማፍራት ዘመናዊ የሆኑ ትጥቅችን በመታጠቅ ጦርነትን ከሩቁ ማስቀረት የሚችል ሰራዊት እየተገነባ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል መሃመድ ተሰማ ስልጣኞች ወደ አሃዳችሁ ስትመለሱ በተሰማራችሁበት የስራ ዘርፍ የተሰጣችሁን ተልዕኮ ከፍተኛ በሆነ ውጤት ግዳጃችሁን በጥራት፣ በኃላፊነት፣ ተጠያቂነትና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ መፈጸም ይገባችኋል ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሌተናል ጀኔራል መሐመድ  ተሰማ ሰራዊቱ  ህገ-መንግስቱን በፅናት በመያዝ የተቋማችንን ተልዕኮ ፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ባህሪያትና እሴቶች በመተግበር እና በማስተግበር የአመራር ሚናቸዉን መወጣት እንደሚገባቸው ተናግረዋል ።

ዘጋቢ አወል መሃመድ

ፎቶ ግራፍ ሳምሶን ባህሩ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ