የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም.
የልዩ ዘመቻዎች ማሰልጠኛ ማዕከል መሠረታዊ ኮማንዶዎችን አሰልጥኖ ለ43 ጊዜ አስመርቋል።
ካራማራ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የመሠረታዊ ኮማንዶ ሰልጣኝ አባላቱ የተለያዩ ወታደራዊ ትርኢቶችን በማሳየት ብቃታቸውንም አረጋግጠዋል።
የ43ኛው ዙር የኮማንዶ ሰልጣኞች ምረቃ ስነስርዓት የሰልጣኞቹ ጥንካሬና ብቃት ጎልቶ መታየቱን የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል።
ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ሰልጣኞቹ የሚሰጣቸውን ማንኛውንም ውስብስብ ግዳጅ እንኳን ቢሆን ሊዋጡ የሚችሉ የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የልዩ ሀይል አባላት ማፍራታቸውን ተናግረዋል።
አዛዡ አክለውም ማሰልጠኛው የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉን የሚያጠናክሩ ለቀጣይም ሀገራዊ ተልዕኮ ዝግጁ የሆኑ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል የማጠናከርና የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ተመራቂ አባላቱ የቀይ መለዮ አለባበስ ስነ ስርዓቱም በጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የለበሱ ሲሆን ሀገራቸውን በቅንነት ለማገልገል ያላቸውን ቁርጠኝነት በቃለ-መሀላ አረጋግጠዋል።
በራሔል ገዛኸኝ