የኮማንዶ ክፍለጦር ለሰላም አልገዛም ባለው የፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ክፍለጦር በኤፍራታና ግድም ወረዳ ዳጉች የሚባል አካባቢ በመመሸግ ህዝቡን ሲዘርፍና ሲያሰቃይ በነበረዉ የፅንፈኛ ቡድን ስብስብ ላይ በወሰደው እርምጃ በቅፅል ስሙ ቀጭኔ  በመባል የሚታወቀዉን የቡድኑ ከፍተኛ አመራር ከነ ጀሌዎች ጭምር በመደምሰስ ቀሪዎችን ማርኳል፡፡

ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ላይ በወሰደው እርምጃ የፅንፈኛውን አባላት ጨምሮ ከህብረተሰቡ የተዘረፈ አንድ አይሱዙ ተሽከርካሪ፣ የተለያዩ ዓይነት መሣሪያ እና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር አውሏል።

የኮማንዶ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል አበባዉ ሞላ አፕሬሽኑ የተፈፀመዉ በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርቶ መሆኑን ገልፀዉ ቡድኑ በዚህ ኦፕሬሽን ብቻ ሳይሆን በሌሎችም በተከታታይ በተወሰዱበት እርምጃዎች አከርካሪዉ ተሰብሮ አለኝ የሚለዉ መዋቅሩ ፈራርሶ የፌስቡክ አርበኛ ሆኖ መቅረቱን ተናግረዋል።

የሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ተስፋየ በላይነህ ፣ ሻለቃ ግዛቸዉ ዘሪሁን እና ሻምበል ግዛቸዉ ጊሎ እንደገለፁት ግዳጁ የተፈፀመበት አካባቢ የተፈጥሮ መሰናክል የበዛበት ለሰራዊቱ አመቺ ያልሆነ መልክዓ ምድር ቢሆንም ሠራዊቱ ፈታኝ የነበረውን የተፈጥሮ መሰናክል ሁሉ በማለፍ ስኬታማ ስራ መስራት ችሏል፡፡

ቀጣይም የፅንፈኛው ስብስብ ወደ ሠላም እስካልመጣ ድረስ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የህዝብን ሠላም ለማረጋገጥ እንደሚሠራ ኮሎኔል አበባው ሞላ ተናግረዋል። ዘገባው የክፍለጦሩ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ