የኮማንዶ ክፍለጦር ለሰላም አልገዛም ባለው የፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ክፍለጦር በኤፍራታና ግድም ወረዳ ዳጉች የሚባል አካባቢ በመመሸግ ህዝቡን ሲዘርፍና ሲያሰቃይ በነበረዉ የፅንፈኛ ቡድን ስብስብ ላይ በወሰደው እርምጃ በቅፅል ስሙ ቀጭኔ  በመባል የሚታወቀዉን የቡድኑ ከፍተኛ አመራር ከነ ጀሌዎች ጭምር በመደምሰስ ቀሪዎችን ማርኳል፡፡

ክፍለጦሩ በፅንፈኛው ላይ በወሰደው እርምጃ የፅንፈኛውን አባላት ጨምሮ ከህብረተሰቡ የተዘረፈ አንድ አይሱዙ ተሽከርካሪ፣ የተለያዩ ዓይነት መሣሪያ እና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር አውሏል።

የኮማንዶ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል አበባዉ ሞላ አፕሬሽኑ የተፈፀመዉ በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርቶ መሆኑን ገልፀዉ ቡድኑ በዚህ ኦፕሬሽን ብቻ ሳይሆን በሌሎችም በተከታታይ በተወሰዱበት እርምጃዎች አከርካሪዉ ተሰብሮ አለኝ የሚለዉ መዋቅሩ ፈራርሶ የፌስቡክ አርበኛ ሆኖ መቅረቱን ተናግረዋል።

የሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ተስፋየ በላይነህ ፣ ሻለቃ ግዛቸዉ ዘሪሁን እና ሻምበል ግዛቸዉ ጊሎ እንደገለፁት ግዳጁ የተፈፀመበት አካባቢ የተፈጥሮ መሰናክል የበዛበት ለሰራዊቱ አመቺ ያልሆነ መልክዓ ምድር ቢሆንም ሠራዊቱ ፈታኝ የነበረውን የተፈጥሮ መሰናክል ሁሉ በማለፍ ስኬታማ ስራ መስራት ችሏል፡፡

ቀጣይም የፅንፈኛው ስብስብ ወደ ሠላም እስካልመጣ ድረስ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የህዝብን ሠላም ለማረጋገጥ እንደሚሠራ ኮሎኔል አበባው ሞላ ተናግረዋል። ዘገባው የክፍለጦሩ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ስፖርት

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ