ኢትዮጵያ በተለያዬ ዘመናት የገጠሟትን ፈተናዎች ሁሉ በድል የተወጣችው በጀግኖች ልጆቿ መሰዋዕትነት ነው። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ  

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

አየር ሃይል፣ ሳይበርና ሜካናይዝድን በማዘመን ወጊያን በመሳሪያ ቴክኖሎጅ እና በውሰን የሰው ሀይል የመጨረሰ አቅም ተገንብቷል ሲሉ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናግረዋል። የሜካናይዝድ ዕዝ ያሰለጠናቸውን የሜካናይዝድ ሙያተኞች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በምረቃ ሰነ-ሰርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣በአዋሽ አርባ ወጊያና ቴክኒክ ትምህርት ቤት ሲሰለጥኑ የቆዩ የሜካናይዝድ ዕዝ ሙያተኞችን  የተኩስ ወጤት ተመልክተዋል።

መከላከያ እንደ ግብ አስቀምጦ ካከናወናቸው የሪፎርም ስራዎች መካከል የመከላከያ ሠራዊቱን አቅም በክህሎት እና ዘመኑ ባፈራቸው ትጥቆች በራስ አቅም አዘምኖ ሠራዊቱ ማንኛውንም ግዳጅ በድል እንዲወጣ ማድረግ አንዱ አቅጣጫ እንደነበር አውስተው ይህም ውጤታማ በሆነ አግባብ በተግባር መረጋገጡን ገልፀዋል።

ዛሬ በሜካናይዝድ ዕዝ ሰልጣኞች የታየው ሁሉን አቀፍ  የማድረግ አቅምና ብቃትም የተቋሙ እቅድ አንድ አካል መሆኑን አሰገንዝበዋል።ኢትዮጵያ በተለያዬ ዘመናት የገጠሟትን ፈተናዎች ሁሉ በድል መወጣት የቻለችው በጀግኖች ልጆቿ መሰዋዕትነት ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ   ይህ የአሸናፊነት ሰነ -ልቦና  ዛሬም በእያንዳንዱ ወታደር ልቦና ወሰጥ መኖሩን ገልፀዋል።

መንግሰት በወሰደው የፀጥታ ተቋማትን የማደራጀትና የመገንባት ሰራ መከላከያ ዘመኑ ያፈራቸውን ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን በራስ አቅም በማምረት በማስታጠቅና መጠቀምና መምራት የሚችል በተግባር

ተፈትኖ ያለፈ በቂ የሰው ሃይል መገንባቱንም አረጋግጠዋል።

ሜካናይዝዱን በማዘመንና በማቀናጀት ውጊያን በዘመናዊ የጦር መሳሪያ በትንሽ የሰው ሃይል ለመጨረስ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱንም ገልፀዋል ። ዛሬ የታየው ወጤትም  ጠላቶቻችን ደጋግመው እንዲያስቡ የሚያደርግና ጦርነትን በሩቁ ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑን ገልፀው ተቋሙን ያደራጀነውም  አሁናዊ የአለም የጦርነት ባህሪን ግምት ውሰጥ በማስገባት ነው ብለዋል።

ማሩ ግርማይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ስፖርት

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ