የጦር መሳሪያ ማስተኮሽያ ሶፍትዌር ያበለፀጉ የፈጠራ ጥበበኞች

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

መሠረታዊ ወታደር ዘላለም ቤዛነህ እና መሰረታዊ ወታደር ዳንኤል ሙልቀን ይባላሉ። ሁለቱ ወጣት ወታደሮች ምንም እንኳን የልጅነት መንገዳቸው የተለያየ ቢሆንም በሀገር ፍቅር ማዕበል የተሳሰሩ ጓደኛሞች ናቸው።

ሁለቱ መሠረታዊ ወታደሮች የጀግኖች ልጆች  በአባቶቻቸው የጀግንነት ታሪክ ተኮትኩተው ያደጉ ናቸው። የሀገር ፍቅር በደም ስራቸው ገብቶ ለወታደርነት ሙያ ያላቸው ክብር ከልጅነታቸው ጀምሮ ሲያብብ መኖሩን ይናገራሉ። ሁለቱም የማወቅ ጉጉት የሞላባቸው ማንኛውንም ነገር የመመራመር ፍላጎት ያላቸው ልጆች ናቸው። እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ ማንኛውንም ነገር መነካካት ይወዱ ነበር።ትምህርታቸውን በሚገባ ተከታትለው አጠናቀዋል። በተለይ ዳንኤል በኮምፒውተር ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪውን በውጤት አጠናቋል። ነገር ግን የሀገር ፍቅርና የአባቶቻቸው የጀግንነት ታሪክ በልባቸው ውስጥ ነግሶ የተማሩበትን እውቀት ለሀገር ክብር ለመጠቀም ወሰኑ።

በአዋሽ አርባ ውጊያና ቴክኒክ ትምህርት ቤት ለሜካናይዝድ ስልጠና ሲገናኙ የጋራ ፍላጎታቸውና የሀገር ፍቅራቸው ወዲያውኑ አቀራረባቸው። በማሰልጠኛው ቆይታቸውም ከመደበኛ ስልጠናቸው ጎን ለጎን የቴክኒክ ችሎታቸውን በማጣመር የጦር መሳሪያ ማስተኮሽያ ሶፍትዌር አበለፀጉ ይህንንም ፈጠራ ለመሪዎቻቸው አቀረቡ ውጤታማነቱም ተረጋገጠ።

ይህ ሶፍት ዌር ለማሰልጠኛውም ለተቋሙም ትልቅ የፈጠራ ውጤት እንደሆነ የታመነበት ሲሆን ሁለቱንም በጀግንነታቸውና በፈጠራ ችሎታቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦ በምረቃ ስነ-ስርዓታቸው ዕለት የሙሉ አስር አለቅነት ማዕረግ ከጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተበርክቶላቸዋል።እነዚህ ወጣት አሥር አለቆች የቴክኖሎጂ እውቀትንና የሀገር ፍቅርን በማጣመር ለአገራቸው እድገት አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሚቻል በማሳየት አርአያነት ያለው ተግባር ለመከወን ችለዋል።

አሥር አለቃ ዘላለም ቤዛነህ እና አሥር አለቃ ዳንኤል ሙልቀን የተሰጠን ማዕረግ ከእድገቱ በተጨማሪ ከባድ ሀገራዊ ሀላፊነት በመሆኑ ለበለጠ የፈጠራ ስራ እንተጋለን ሲሉ አጫውተውናል።

አሥር አለቆቹ በጀግንነታቸው፣ በፈጠራ ችሎታቸውና በጓደኝነታቸው የሚታወሱ ለወጣት የሠራዊት አባላትም አርአያነት ያለው ተግባር የሰሩና ተቋማችንም የዕውቀት ማዕከል እንደሆነ ያመላከቱ ጀግኖች ናቸውና ነገም በዙ እንደሚሠሩ እምነታችን ነው።

በልደት አስረስ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com

@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ