በትጥቅ የመከላከያ ሠራዊቱን የዝግጁነት ደረጃ ለማሣደግ እየሠራን ነው  አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

በትጥቅም ሆነ በትጥቅ ግብዓቶች የመከላከያ ሠራዊቱን የዝግጁነት ደረጃ ለማሣደግ በውጤት እየሠራን ነው ሲሉ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ተናገሩ

ቆየት በሚል ስያሜው የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በሚል ሲጠራ የነበረው አሁን ላይ ተቋሙ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 567/2017 በመፅደቁ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ በመባል አድማሱን በማስፋት በርካታ ኢንዱስትሪዎችን አካቷል።

ለመከላከያ ሠራዊት የተለያዩ ትጥቆችን እና የትጥቅ ግብዓት ምርቶችን በማምረት እና የተለያዩ የኮሜርሻል ምርቶችን በማምረት እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር ብቸኛው ተቋም ከመሆኑ አንፃር ትልቅ የሃይል አቅም በመሆን ዘርፈ ብዙ በቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራትን እያከናዎነ እንደሚገኝ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ገልፀዋል።

መንግስትና ተቋሙ ለመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠታቸው በሪፎርሙ አዳዲስ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም የምርትና ምርታማነትን በማምረት የሠራዊቱን የዝግጁነት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ኮሎኔል ዩሃንስ ትኬሳ በበኩላቸው እየተመዘገበ ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለተቋሙ ብሎም ለሀገራችን ከፍታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

የመከላከያን ፍላጎት ለማሟላት የኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፑ አመራርና ሠራተኛ በአንድ እስትንፋስ ምርትና ምርታማነትን በማሣደጉ ረገድ ሥራቸውን በአግባቡ በመፈፀም ሀገራዊ ተልዕኳቸውን በስኬት የመወጣቱን ሂደት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ኮሎኔል ዩሃንስ ተናግረዋል።

በመስከረም ብርሃኔ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ስፖርት

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ