የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ይቻላልን  በተግባር ያረጋገጠ ተቋም ነው። ወይዘሮ ማርታ ሉዊጂ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል በይፋ ተመርቆ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የሠራዊቱን የጤና አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን እና ከፍ ወዳለ ደረጃ በማሸጋገር ውጤታማ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስቴር ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ማርታ ሉዊጂ ተናግረዋል።

‎ሚኒስትር ዲኤታዋ ሆስፒታሉ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ በየጊዜው የሚያስደምም ውጤት እያስመዘገበ ይቻላልን በተግባር እያረጋገጠ የሚገኝ ተቋም እንደሆነ ጠቁመው ለዚህም በቅርቡ ለሰራዊቱ የተደረገው የዳሌ መገጣጠሚያ አጥንት ቅየራ ህክምና አንዱ ማረጋገጫ እንደሆነም አረጋግጠዋል።ይህ ደግሞ በየደረጃው የሚገኝ አመራር ሙያተኛ እና ባለ ድርሻ አካላት በጋራ በመተባበር እና በመደጋገፍ በመስራታችሁ የተገኘ ውጤት ነው ልትመሰገኑ ይገባልም ብለዋል

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ በበኩላቸው ሆስፒታሉ እንደ ሀገር እና እንደ ተቋም የተቀመጠውን የዘመናዊ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ግብ ሊያሳካ የሚችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል ።

በቀጣይም ሆስፒታሉን በዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች እና ሙያተኞች በማሟላት በአፍሪካ ውስጥ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ የህክምና ማዕከል እንዲሆን የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። አሁን ላይ የተሰራው የዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራም ይህንን ተግባር የሚያረጋግጥ እንደሆነም አንስተዋል ።

‎በተጨማሪም ምንግዜም ስራዎች አመራሩ ችግር ፈች የሆኑ ውሳኔዎች እየሰጠ እና የጤና ሙያተኛው ደግሞ በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት መስራት ከተቻለ የማይቻል ነገር እንደሌለ ያረጋገጠ ተግባር ፈጽማችኋልና ተቋሙም ሀገርም ይኮራባችኋለች ነው ያሉት ጄኔራል መኮኑ።

‎የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ሸዋዬ ኃይሌ ሆስፒታሉ በ2017  በጀት አመት በታቀደው እቅድ መሰረት ከመከላከያ የፋይናንስ ዘርፍ ጋር በመነጋገር አስፈላጊው በጀት እንዲፈቀድ በማድረግ ከ685 በላይ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን ከውጭ ሀገር በማስገባት እና በማስገጠም ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል ።

ከዚህ ጋር ተያይዞም 104 የሚሆኑ የመገጣጠሚያ አጥንት ጉዳት የደረሰባቸውን የሠራዊት አባላትን ተቀብለው ለ53 አባላት የተሳካ ህክምና መደረጉን ተናግረዋል። ታካሚዎቹም በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ለቀሩት ታካሚዎችም የዳሌ እና የመገጣጠሚያ አጥንት ቅየራ ህክምናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል ።

‎ሆስፒታሉ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ ድጋፍ እና ትብብር ላደረጉላቸው አካላት በሆስፒታሉ ለሚሠሩ ሙያተኞች እና ሠራተኞች ለባለ ድርሻ አካላት በሙሉ በሆስፒታሉ እና በራሳቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

በኤሊያስ ከለለኝ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ