የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን ዳግሚዊ ሚኒልክ ሆስፒታልን 3ለ0 አሸነፈ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስፖርት ለሁሉም አዘጋጅነት እየተሳተፈ የሚገኘው የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን የዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታልን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የማሸነፊያ ጎሎቹን አምሳ አለቃ በሃይሉ አለባቸው ፣ አስር አለቃ ምህረትኣብ ማቲዮስ እና መሠረታዊ ወታደር እስክንድር ሰለሞን አስቆጥረዋል።

በሁለት ምድብ ተከፍሎ እየተካሄደ በሚገኘው የአንደኛ ዲቪዚዮን የጤና እግር ኳስ ቡድን መቻል ምድቡን በበላይነት በማጠናቀቅ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል።

የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን ካደረጋቸው ሰባት የምድብ ጨዋታዎች አምስቱን አሸንፎ ሁለቱን አቻ በመለያየት 17 ነጥብ እና 20 ተጨማሪ ጎል በመያዝ ምድቡን በአንደኝነት ማጠናቀቅ ችሏል።

የጤና እግር ኳስ ቡድን ከተለያዩ የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎች ተወጣጥተው በመቻል ስፖርት ክለብ ደጋፊነት ተቋሙን በመወከል በኢፌዴሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር እና በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋቻቸው ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።

የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን ያለፈውን አመት በተወዳደረባቸው ሶስት ውድድሮች ሁሉንም ዋንጫዎችን በማሸነፍ የተቋሙን ስም ማስጠራት ችሏል።

ዘጋቢ ገረመው ጨሬ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629…

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ