የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም
ከመከላከያ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥነ ልቦና ግንባታ አመራሮች እና የሚዲያ ሙያተኞች ሲሰጥ የቆየው ሰልጠና ተጠናቋል። በዚሁ የሰልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰራዊት ሰነ- ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰራዊታችን የተሠጠውን ሀገራዊና ህዝባዊ አደራ መሠረት አድርጎ የሚያከናውነው ህዝባዊና ሀገራዊ ተልዕኮ በሚገባ አልተነገረለትም ብለዋል።
ይህንን አካሄድ ለማስተካከል የሰራዊቱን ልፋትና ድካም የሚረዱ በእያንዳንዱ ግንባር ድል ያደረጉ ብዕርና ወረቀታቸውም የጠላትን ሀሰታዊ ፕሮፖጋንዳ ከንቱ የሚያስቀር ጀግና ወታደራዊ ጋዜጠኞች ማፍራት ላይ
ትኩረት በማድረግ እየተሠራ ሥለመሆኑ አንስተዋል።
የሠራዊታችንን ሰነ ልቦና በውጊያም ሆነ ከውጊያ በኃላ ሳይቆራረጥ ተከታታይ በሆነ መልኩ መሰራት ያሥፈልጋል ያሉት ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ይህ የሚሆነውም የስነ ልቦና ግንባታ የሰራዊታችን የአሸናፊነት ሰንቅ ሰለሆነ ነው ብለዋል።
ሰራዊቱ የሚፈፅመው አኩሪ ተጋድሎ በሚዲያዎቻችን ለህዝባችን እንዲደርስ በተቋሙ ክፍሎች ያሉ የሚዲያ ሙያተኞች ጠንክረው መስራት አለባቸው ያሉት ጀነራል መኮንኑ ስልጠናው የተሰጠውም ከዚህ አላማ አንፃር መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ አሁን ላይ የሚዲያ ነፃነትን በመጥፎ ጎኑ በመጠቀም የሰራዊታችንን ሰምና ዝና ለማጥፋት የሚጥሩ ሃይሎች ያሉ በመሆናቸው የእነዚህን እኩይ ሃይሎች የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተከታትሎ ማጋለጥ ይገባልም ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያገኛችሁትን አቅም በመጠቀም የሰራዊታችንን የዕለት ተዕለት ተልዕኮና እሱን ተከትሎ የሚያስመዘግበውን አኩሪ ተጋድሎ ለሚዲያ ሽፋን በሚሆን መልኩ መሰነድ ፣ መዘገብ ይጠበቅባችኋል ሲሉም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚን ጨምሮ ለሥልጠናው መሳካት ከፍተኛ አሥተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሜጄር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ምስጋና አቅርበዋል።
አጠቃላይ የሥልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የዋና ዳይሬክቶሬቱ የሥልጠና ቡድን መሪ ኮሎኔል መንግስቱ ካታንጋ ስልጠናው በተመደበለት የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንድፈ ሃሳብና በተግባር ለሥነ ልቦና አመራሮችና ለሚዲያ ሙያተኞች በቀንና በማታ የተሠጠ መሆኑን ጠቁመው ስልጠናው በየክፍላቸው በተግባር ከሚያከናውኗቸው የግንባታ ስራዎች ጋር አያይዘው እንዲመለከቱት መደረጉንም ተናግረዋል፡፡
በማሩ ግርማይ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ