የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

ከመከላከያ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥነ ልቦና ግንባታ አመራሮች እና የሚዲያ ሙያተኞች ሲሰጥ የቆየው ሰልጠና ተጠናቋል። በዚሁ የሰልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰራዊት ሰነ- ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰራዊታችን የተሠጠውን ሀገራዊና ህዝባዊ አደራ መሠረት አድርጎ የሚያከናውነው ህዝባዊና ሀገራዊ ተልዕኮ በሚገባ አልተነገረለትም ብለዋል።

ይህንን አካሄድ ለማስተካከል የሰራዊቱን ልፋትና ድካም የሚረዱ በእያንዳንዱ ግንባር ድል  ያደረጉ ብዕርና ወረቀታቸውም የጠላትን ሀሰታዊ ፕሮፖጋንዳ ከንቱ የሚያስቀር ጀግና ወታደራዊ ጋዜጠኞች ማፍራት ላይ

ትኩረት በማድረግ እየተሠራ ሥለመሆኑ አንስተዋል።

የሠራዊታችንን ሰነ ልቦና በውጊያም ሆነ ከውጊያ በኃላ ሳይቆራረጥ ተከታታይ በሆነ መልኩ መሰራት ያሥፈልጋል ያሉት ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ይህ የሚሆነውም የስነ ልቦና ግንባታ የሰራዊታችን የአሸናፊነት ሰንቅ ሰለሆነ ነው ብለዋል።

ሰራዊቱ የሚፈፅመው አኩሪ ተጋድሎ በሚዲያዎቻችን ለህዝባችን እንዲደርስ በተቋሙ ክፍሎች ያሉ የሚዲያ ሙያተኞች ጠንክረው መስራት አለባቸው ያሉት ጀነራል መኮንኑ ስልጠናው የተሰጠውም ከዚህ  አላማ አንፃር መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ አሁን ላይ የሚዲያ ነፃነትን በመጥፎ ጎኑ በመጠቀም የሰራዊታችንን ሰምና ዝና ለማጥፋት የሚጥሩ ሃይሎች ያሉ በመሆናቸው የእነዚህን እኩይ ሃይሎች የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተከታትሎ ማጋለጥ ይገባልም ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያገኛችሁትን አቅም በመጠቀም የሰራዊታችንን የዕለት ተዕለት ተልዕኮና እሱን ተከትሎ የሚያስመዘግበውን አኩሪ ተጋድሎ ለሚዲያ ሽፋን በሚሆን መልኩ መሰነድ ፣ መዘገብ ይጠበቅባችኋል ሲሉም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚን ጨምሮ ለሥልጠናው መሳካት ከፍተኛ አሥተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሜጄር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ምስጋና አቅርበዋል።

አጠቃላይ የሥልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የዋና ዳይሬክቶሬቱ የሥልጠና ቡድን መሪ ኮሎኔል መንግስቱ ካታንጋ ስልጠናው በተመደበለት የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንድፈ ሃሳብና በተግባር ለሥነ ልቦና አመራሮችና ለሚዲያ ሙያተኞች በቀንና በማታ የተሠጠ መሆኑን ጠቁመው ስልጠናው በየክፍላቸው በተግባር ከሚያከናውኗቸው የግንባታ ስራዎች ጋር አያይዘው እንዲመለከቱት መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

በማሩ ግርማይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com

@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ