በማያቋርጥ የስልጠና ሂደት ያለፈ መሪ ድል አድራጊነት የዘወትር ተግባሩ ነው- ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና

የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

በማያቋርጥ የስልጠና ሂደት ያለፈ መሪ ድል አድራጊነት የዘወትር ተግባሩ ነው ሲሉ ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ገለፁ።

ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና  ይህንን የተናገሩት ለ6ኛ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በሚሰጠው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

ኢትዮጵያ ተጋርጦባት ከነበረው ሃገራዊ አደጋ ወጥታ ፊቷን ወደ ልማት ያዞረችው በሠራዊቱ የተከበረ መስዋዕትነትና የአላማ ፅናት መሆኑን ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ተናግረዋል።

ሠራዊታችን በፕሮፌሽናሊዝም መንገድ የተደራጀውም ሆነ የተዘጋጀው ለሰፈር ሃይሎች ሳይሆን በተሳሳተ ስሌት ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሚሞክሩ የውጭ ሃይሎች ነው ያሉት ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ይህንን አቅም ለማሳደግ ሁለንተናዊ የአለም የጦርነት ባህሪን ግምት ውስጥ ያስገባ ሳይንሳዊ ስልጠና በተከታታይነት ለሠራዊቱ እየተሰጠ ነው ብለዋል።

እየተዋጋን መሠልጠን አንዱ የብቃታችን ማሳያ ነው ያሉት ጀኔራል መኮንኑ ለዘመኑ የሚመጥን እውቀት አስተሳሰብና ችሎታን  መላበስ አሰፈላጊ መሆኑንም አስረድተዋል።

የ6ኛ ዕዝም የማድረግ አቅሙን ወደላቀ ደረጃ በማሸጋገር ከዚህ ቀደም በነበሩ ውጊያዎች ሁሉ የድል አብሪ ኮከብ ሆኖ ተቋምና ሃገርን ማሻገር የቻለ ታሪካዊ ዕዝ ነው ያሉት ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና አሁንም ቢሆን የውጭ ጠላቶቻችንን አጀንዳ ለማስፈፀም በሀገር ውስጥ ሌባና ፖሊስ የሚጫዎቱ የፅንፈኛና የአሸባሪ ሃይሎችን በማክሰም እየተቀዳጀ  የሚገኘውን አኩሪ ድል በቀጣይም የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል።

እነዚህ የጥፋት ሃይሎች ህገ መንግስትና ሃገርን አፍርሰን ስልጣን እይዛለሁ ከሚል ከንቱዋዊ ምኞት የዘለለ አንዳችም ገዥ ሃሳብ የሌላቸው በመሆኑ ህዝቡ ከሠራዊታችን ጎን ሆኖ እየታገላቸውም ይገኛል ብለዋል።

በደባልቅ አቤ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ