የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም
ግዳጁን በፅናት የሚፈፅምና በምንም አይነት ፈታኝ ሁኔታዎች የማይበገር ጠንካራ ሠራዊት ተገንብቷል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።
ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በሠራዊቱ የግዳጅ ቀጠና ተገኝተው ሠራዊቱን ባበረታቱበት ወቅት የኢትዮጵያን ሠላምና ዕድገት የማይሹ ቅጥረኞች በሠራዊታችን ጠንካራ ክንድ የእጃቸውን አግኝተዋል ሲሉ ተናግረዋል።
ለኢትዮጵያ ሠላም የምንከፍለው ዋጋ ያኮራናል ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በተሳሳተ ስሌት የገመገሙን ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ተላላኪ ባንዳዎቻቸው የሃፍረት ካባቸውን ተከናንበዋልም ብለዋል።
በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ክብር መቼም ቢሆን እንደማንደራደር ታሪካዊ ጠላቶቻችን ጠንቅቀው ያውቁታል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ለዚህም ትንኮሳ አድርገው ሠላሟን ለማደፍረስ የተፈታተኗት ሁሉ የደረሰባቸውን ውርደት ያስታውሱታልም ብለዋል።
እኛ ሁሌም አሸናፊ የምንሆነው የቆምንለትን አላማ ጠንቅቀን ስለምናውቅና የኢትዮጵያ ወታደሮች ስለሆንን ነው ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ፅናት፣ቁርጠኝነትና አይበገሬነታችሁ የዚሁ ማረጋገጫም ነው ብለዋል።
በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነን መጪውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ ወታደራዊ ዝግጁነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን፤ ህገመንግስታዊ ተልዕኳችንንም በፅናት እንፈፅማለን ሲሉም ተናግረዋል።
የሠራዊቱ አባላት በበኩላቸው የቀጣናውን ሠላም አሰተማማኝ ለማድረግ በርካታ ስኬታማ ተልዕኮዎችን ስንፈፅም ቆይተናል አሁንም ማንኛውንም ግዳጅና ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈፀም እንደ ግልም ይሁን እንደ አሃድ ዝግጁነታችን ከመቼውም ጊዜ የላቀ ነው ብለዋል።
ዘገባው የአንዷለም ከፍያለው ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ