ራሱን የነዘመነ ቡድን ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛ ለሰሜን ሜጫ አስተዳደር እጅ ሰጠ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

መንግስት ያስተላለፈውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጃቸውን የሰጡት 12 በሰሜን ጎጃም  ጫካ ገብተው የነበሩ አመራሮች ናቸው።

እጅ በሰጠው ቡድን ስር በራሱ አደረጃጀት እራሱን የኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ ብሎ ከሚጠራው መካከል

1. ሻምበል መንግስቱ ድልነሳ አለም –  ሻለቃ አዛዥ

2. መቶ አለቃ ምስጋናው ሽታ ገረመው – ሻለቃ ዘመቻ ሀላፊ

3. ዶክተር አንለይ አሰፋ ዘላለም – በአቸፈር ቀጠና አቤ ጎበኛ ብርጌድ አስተዳደር እና ጸጥታ ሀላፊ እና ሌሎች ስምንት አመራሮች እና አባላቱ መንግሰት የሰጣቸውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እጅ ሰጥተዋል።

በሰላም እጅ ሲሰጡ የሰሜን ጎጃም ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ገብረስላሴ ታዘብ፣ የምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር አመራሮች ፣ የመርዓዊ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ብርሃኑ አበረ፣ የመርዓዊ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታነህ መልኬ ተገኝተዋል።

እጅ ከሰጡት መሐል አንዳንዶቹ እንደተናገሩት ፣ እስካሁን የሄድንበት የተሳሳተ መንገድ በመሆኑ እኛም፣ ቤተሰቦቻችንም እና መላ ህዝባችንም ብዙ ዋጋ ከፍለናል፤ ብዙ ወንደሞቻችን እና እህቶቻችን አጥተናል፤ ተጨማሪ ህይወት መጥፋት የለበትም፤ ነገ ድርድር ቢደረግ የማናገኛቸውን ወጣቶች ማጣት የለብንም ብለን የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን የህዝባችንን መከራ ለማቆም ወስነን እጅ ሰጥተናል ብለዋል።

አሁንም በተሳሳተ መንገድ ላይ ያሉ ወንድሞቻችን የእኛን ፈለግ ተከትለው መንግስት የዘረጋው የሰላም እጅ ሳይታጠፍ ህይወታቸውን ለቤተሰቦቻቸው እንዲያቆዩ ወንድማዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ብለዋል።

በተያያዘ ዜና በአዴት ዙሪያ በዴንሳባታና በአጊታ ቀበሌ የተሰማራው በምስራቅ ዕዝ ስር የሚገኝ አንድ ሬጅመንት በፅንፈኛው ቡድን ላይ በወሰደዉ እርምጃ አስር የጠላት ሀይል ሲደመስስ አንድ መትረየሰ ማርኳል፡፡

የዕዙ የሠራዊት አባላት በተሰማሩባቸዉ የግዳጅ ቀጠናዎች የሰላምን አማራጭ ባልተቀበሉ የፅንፈኛው ቡድን ላይ እግር በእግር እየተከታሉ የመደምሰሱን ተግባር አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

ሰሞኑን በአዴት ዙሪያ በዴንሳባታና በአጊታ ቀበሌ ከጠላት ጋር የተደረገዉን ኦፕሬሽን አስመልክተው የአንድ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ባሻ ፈንታሁን አሰፋ እንደተናገሩት፣ በነበረን ስምሪት ጠላትን ከገባበት ገብቶ በማሳደድ ጠንካራ ምት አሳርፈንበታል፤ በዚህም ዘመቻ አስር የጠላት ሀይል በመደምሰስ 12 በማቁሰል ፣ አንድ ፒ ኬ ኤም/መትረየስ ፣ አንድ ባለ 100 የመትረየስ ሸንሸል፣ ሁለት ክላሽ ፣ ሁለት ካዝና ፣ ሰባት ቃታ መሳሪያ ፣ አንድ የስናይፐር መነፅር እና 187 ተተኳሽ ጥይት ማርከናል ብለዋል፡፡

በተሰለፍንበት የግዳጅ ቀጠና የአካባቢዉ ህብረተሰብ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ እና ወደ  መሰረተ ልማት የበለጠ ትኩረቱን አድርጎ እንዲሰራ የምናደርገዉን የጠላት ሀይል ለይቶ የመደምሰስ ግዳጃችንን ከአካባቢዉ ህብረተሰብና የፀጥታ አካላት ጋር አቀናጅተን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ ታደሰ ይሴ

ፎቶግራፍ ከሬጅመንት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ