ሴት የሠራዊት አባላት በአመራር ሰጪነታቸው ብቁ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

በደቡብ ዕዝ አዘጋጅነት ከዕዝ ስታፍ፣ ከኮር እንዲሁም፣ ከክፍለጦር ለተውጣጡ ሴት የሠራዊት አባላት በወታደራዊ አመራርነት ሚና እና ክህሎት ብሎም በስርዓተ ፆታ አቅም ግንባታ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና ለሁለት ቀናት ተሠጥቷል።

በስልጠናው ማጠቃለያ የተገኙት የመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ወታደራዊ አመራርነት ማለት ጀግንነት፣ ሙያዊ ብቃት እና የሠራዊት እሴቶችን መላበስ መሆኑን በማንሳት ሴት የሠራዊት አባላት እነዚህን ነገሮች ለማግኘት በብቃት ፈተናዎችን መቋቋም እና ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

በመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት የስርአተ ፆታ ማካተት ቡድን መሪ ወይዘሮ አስተዋይ  ሳሙኤል ሴቶች ካለባቸው የስራ ጫና እና የበታችነት ስሜቶች መላቀቅ እንደሚገባቸው ገልፀው ወደ መሪነት ለመምጣት አስፈላጊውን ሁሉ አቅም መጨበጥ  እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። 

የደቡብ እዝ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ ኮሎኔል ፋንታነሽ ሞላ የተዘጋጀው ስልጠና ሴትነትን እና መሪነትን በመገንዘብ ቀጣይ ለሚጠብቅ የመሪነት ሚና ራስን ማብቃት እና ማዘጋጀት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር በመግለፅ በክፍላቸው ግዳጅ እየተወጡ ባለበት ግዜ ከፍተኛ ጀብድ ለፈፀሙ ሴቶች ሽልማት በመሸለም የስልጠና መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

ዘጋቢ እዮብ ሰለሞን

ፎቶግራፍ አብረሀም ወርቁ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ