የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም
በደቡብ ዕዝ አዘጋጅነት ከዕዝ ስታፍ፣ ከኮር እንዲሁም፣ ከክፍለጦር ለተውጣጡ ሴት የሠራዊት አባላት በወታደራዊ አመራርነት ሚና እና ክህሎት ብሎም በስርዓተ ፆታ አቅም ግንባታ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና ለሁለት ቀናት ተሠጥቷል።
በስልጠናው ማጠቃለያ የተገኙት የመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ወታደራዊ አመራርነት ማለት ጀግንነት፣ ሙያዊ ብቃት እና የሠራዊት እሴቶችን መላበስ መሆኑን በማንሳት ሴት የሠራዊት አባላት እነዚህን ነገሮች ለማግኘት በብቃት ፈተናዎችን መቋቋም እና ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።
በመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት የስርአተ ፆታ ማካተት ቡድን መሪ ወይዘሮ አስተዋይ ሳሙኤል ሴቶች ካለባቸው የስራ ጫና እና የበታችነት ስሜቶች መላቀቅ እንደሚገባቸው ገልፀው ወደ መሪነት ለመምጣት አስፈላጊውን ሁሉ አቅም መጨበጥ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
የደቡብ እዝ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ ኮሎኔል ፋንታነሽ ሞላ የተዘጋጀው ስልጠና ሴትነትን እና መሪነትን በመገንዘብ ቀጣይ ለሚጠብቅ የመሪነት ሚና ራስን ማብቃት እና ማዘጋጀት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር በመግለፅ በክፍላቸው ግዳጅ እየተወጡ ባለበት ግዜ ከፍተኛ ጀብድ ለፈፀሙ ሴቶች ሽልማት በመሸለም የስልጠና መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።
ዘጋቢ እዮብ ሰለሞን
ፎቶግራፍ አብረሀም ወርቁ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ