የሀገራችንን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሰራዊቱንና የአመራሩን ብቃት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

 ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ በአጭር ኮርስ ያሰለጠናቸውን የክፍለ ጦር አመራሮችን አስመረቋል።

በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ሀላፊ ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን ባስተላለፉት መልዕክት ወቅታዊ ፣ ውስጣዊ ፣ ቀጠናዊና አካባቢያዊ ሁኔታዎችን የተረዱ ብቻ በሳይንሳዊ መልኩ የሚተነብዩ አመራሮችን ለማፍራት የኮሌጁ ሚና የላቀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አመራሮቹ በተግባራዊ ውጊያ የተፈተኑና የውጊያ ልምድ ያላቸው መሆኑን የጠቀሱት ሀላፊው ስልጠናው  ተለዋዋጭ ወታደራዊ ሁኔታዎች እንዲገነዘቡ ያደረገ ተግባር ተኮር ስልጠና መሰጠቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።

መከላከያ የሀገራችንን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ዘመናዊ፣ ፕሮፌሽናልና ዲሲፒሊንድ የሆነ ሰራዊት ለመገንባት እያደረገ ያለው ጥረት ውጤታማ መሆኑን ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዘመናችን ውጊያዎች ውስብስብ ፣ ዘመናዊና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የሚጠይቁ መሆናቸውን የገለፁት ሀላፊው፣ ለዚህም ያልተቋረጠ ስልጠና ወሳኝ መሆኑንና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም  ገልፀዋል።

ተመራቂ ከፍተኛ መኮንኖቹ ያላቸውን የረጅም ጊዜ የውትድርናና የአመራር ልምድ ካገኙት ስልጠና ጋር በማዋሀድ አሀዶቻቸውን ማደራጀት ማብቃትና በተፈለገው ጊዜና ቦታ የሚሰጣቸውን ግዳጅ በመፈፀም ሀገራቸውን ማኩራት እንደሚኖርባቸውም አሳስበዋል።

በዝግጅቱ ላይ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ምክትል ሀላፊ ለአመራር ስልጠና  ሜጀር ጀነራል ሰለሞን  ቦጋለን ጨምሮ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮችና የኮሌጁ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።

በብዙአየሁ ተሾመ

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ስፖርት

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ