የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን የአንደኛ ዲቪዚዮን የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት አዘጋጅነት ከጥር 04 ቀን እስከ ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው የአንደኛ ዲቪዚዮን በመቻል ሁለተኛ ዲቪዚዮን በአቃቂ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ  አሸናፊነት ተጠናቋል።

በመዝጊያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ለአሸናፊ ቡድኖች የዋንጫ እና ሜዳሊያ የሠጡት የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፕሬዘዳንት የእሳት እና ድንገተኛ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አህመድ መሃመድ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ናቸው።

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ መቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን የሚኒሊክ ሆስፒታል አቻውን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። መቻል ባለድል የሆነበትን ሶስቱንም ጎሎች አስር አለቃ አንተነህ ጌታቸው ከመረብ አሳርፏል።

የውድድሩ ኮከብ አሰልጣኝ የመቻሉ ሻምበል ወንደወሰን በየነ ሲሆን ፣ 10 ጎሎችን በማስቆጠር መቶ አለቃ ደረጄ ግዛው ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ፣ አምሳ አለቃ ግርማ ገቢሳ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ሶስቱም ከመቻል አሸናፊ በመሆን ሽልማታቸውን ከክብር እንግዶች ተረክበዋል ።

የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን በሃልም ኢንተርናሽናል እና በአንበሳ ስፖርት ትጥቅ አምራች ስፖንሰር አድራጊነት በተደረገው የእግር ኳስ ውድድር በይቻላል አንድ ለዜሮ ተሸንፈው ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ የብር ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል።

ወድድሩ የሚቀጥል ሲሆን በ18ኛው የመንግስት መስሪያ ቤቶች የእግር ኳስ ውድድር መከላከያ ሠራዊት እግር ኳስ ቡድን ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር ሰኞ ሰኔ 01 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም የፍፃሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በተያያዘ ዜና የመቻል ከ17 ዓመት በታች የሮሃ አቻውን 8ለ0 በሆን ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

በገረመው ጨሬ

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ