የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ክብሯን ጠብቆ ማሻገር የእኛ ትውልድ ኃላፊነት ነው።

        ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ክብሯን ጠብቆ ማሻገር የኛ ትውልድ ኃላፊነት ነው ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።

ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በአንድ ኮር  በስልጠና ላይ የሚገኙ የመቶና የጓድ አመራሮች የስልጠና ሂደትን በተመለከቱበት ወቅት ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ክብር መስዋዕትነት ክብሯ ተጠብቆ ዛሬ ላይ ደርሳለች በእኛ ትውልድም የአፍሪካዊያን ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት ሆና ትቀጥላለችም ብለዋል።

ኮሩ ፅንፈኛውን ቡድን በመደምሰስ ተልዕኮውን በላቀ ጀግንነት የፈፀመ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ሠራዊቱን በመምራት፣በማስተባበር ራሳችሁም ጭምር ተዋጊ በመሆን አኩሪ ገድል ፈፅሟችኋልም ብለዋል።

ሠራዊቱን በሁለንተናዊ መስክ ለማብቃት የቅርብ አመራሩ ድጋፍና ክትትል ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ብቃት ያለው የመቶና የጓድ አመራር ለጠንካራ ሠራዊት ግንባታ መሠረት ስለመሆኑም ተናግረዋል።

ተቋማችን ለሠራዊት ግንባታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት ይገኛል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከዘመኑ ጋር እየዘመነና በቴክኖሎጂ አቅሙ እያደገ በመምጣቱ ለኢትዮጵያ ክብር የሚመጥናት የመከላከያ ኃይል በመገንባት ላይ ስለ መሆኑም ተናግረዋል።

በየደረጃውና በየተመደብንበት የስራ መስክ ውጤታማ ስንሆን የፕሮፌሽናል ሠራዊት ግንባታውን እውን እናደርጋለን ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በስልጠና የሚፈጠር ሁለንተናዊ  አቅም ለቀጣይ ተልዕኮ ስኬት የበለጠ የሚያዘጋጅ  መሆኑን በመገንዘብ ለውጤታማነት መትጋት ይጠበቅባችኋል  ሲሉም አሳስበዋል።  

በአንዷለም ከፍያለው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ስፖርት

IMG_20250620_160750_199
ኢትዮጵያና አሜሪካ በሠላምና በፀጥታ ጉዳይ በጋራ የመስራት ልምዳቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
IMG_20250620_202021_755
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የምትወጣውን በጎ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ።
IMG_20250622_130413_910
ሠራዊቱ የታጠቀውን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች በጥናትና ምርምር ማሳደግ ይገባል
IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ