ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 03 ቀን 2017 ዓ.ም

በጠቅላይ መምሪያው የጠቅላላ አገልግሎት ዋና ዳይሬክቶሬት በተሠጠው ዝርዝር ሃላፊነቶች መሠረት ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ እንደሚገኝ የዋና ዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር ገለፁ።

አሠራርና መመሪያው በሚያዘው መሠረት የሠራዊቱን የመኖሪያ ቤትና የሥራ መገልገያ ቢሮዎችን ማመቻቸት ፣እንደ ውሃ መብራትና ሌሎች አገልግሎት መሥጫዎችን መከታተል እንደአሥፈላጊነቱ የመጠገንና ለአገልግሎት ምቹ የማድረግ ሥራዎች በክፍሉ እየተከናወነ ሥለመሆኑ አሥረድተዋል።

የካምፖችና ቤቶች አሥተዳደር ከቤት ዕደላና ከጥገና ሥራዎች ጋር በተያያዘ አሥፈላጊውን ክትትል እያደረገ ሥለመሆኑ የተናገሩት ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር እየተጠናቀቀ ባለው የ2017 በጀት ዓመት ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶች ለሠራዊት መታደላቸውንና የመኖሪያ ቤት እጥረትን ሊቀርፉ የሚችሉ በርካታ ቤቶች በካምፖች በተለይም ደግሞ በጎፋ ካምፕ እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ሠራዊቱንና ቤተሠቡን ከመደጎም አንፃር በመደብሮችና መዝናኛ ክበቦች አማካኝነት በርካታ ችግር ፈች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልፀዋል። በአነስተኛና ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ እንደ ዘይት ስኳር ፊኖ እና መሠል የሸቀጣሸቀጥ ፍጆታዎች ለሠራዊቱ ተደራሽ እንደሚሆኑና ክበቦች በአነስተኛ ዋጋ ለሠራዊቱ አሥፈላጊውን የምግብ አገልግሎት እንደሚሠጡም አንስተዋል።

የወተት ላሞች በማርባት በየካምፑ ለሠራዊቱ የወተት አቅርቦት ማከናወን፣ በጠቅላይ መምሪያው በሚገኘው ሀይቅ ዓሣ በማሥገር ለሠራዊቱ ክፍሎች ማድረስ፣ የዶሮ እርባታ በሠፊው መሣተፍ ፣እንቁላል ለተጠቃሚው ማድረስ እና መሠል ሥራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ የሠራዊቱንና ቤተሠቡን ኑሮ መደጎም እየተቻለ መሆኑን እና ቀጣይ ይበልጥ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር አረጋግጠዋል።

ዘጋቢ ውብሸት ቸኮል

ፎቶግራፍ ደጀኔ አሳይቶ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ስፖርት

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ