በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-

   ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመከላከያ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ መከላከያ ሠራዊቱ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በትብብር ለመስራትና በጋራ ለመበልጸግ ያላሳለሰ ጥረት እያደረገች እንደምትገኝ አንስተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት እንዲሁም የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚያስከብር ሠራዊት መገንባቱን ነው ያስገነዘቡት፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ  በበኩላቸው÷ የተቋሙን የማስፈጸም አቅም በማጎልበት ሀገርና ሕዝብን ከማንኛውም ጥቃት የመከላከል ሥራ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ተዓማኒነት ያለው ነጻና ገለልተኛ ወታደራዊ የፍትህ ዳኝነት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው ÷ የሠራዊቱን አስተማማኝ የሎጂስቲክስ ክምችት ማሟላት መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ስፖርት

IMG_20250615_181715_464
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሠጡት ማብራሪያ እና በምዕራብ ዕዝ ኮር ምሥረታ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፦
IMG_20250615_143244_103
ሠራዊቱ አስተማማኝ የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል   ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
IMG_20250615_125428_873
የመከላከያ ሠራዊት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው
IMG_20250615_091554_004
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነት እያረጋገጥን ለግንባታውም አስተዋጽኦ እያደረግን ነው
IMG_20250611_174829_584
በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል-
IMG_20250610_183711_398
ዋና ዳይሬክቶሬቱ ሠራዊቱንና ቤተሠቡን በፍትሃዊነት እያገለገለ ነው።   ሜጄር ጄኔራል አብዱ ከድር

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ