የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም
በአፍሪኮም ዕዝ አዛዥ ጀነራል ሚካሄል ላንግሌይ የተመራ ልዑክ ከጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ጋር ያደረጉትን ውይይት አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዳይሬከተር ሜጀር ጀነራል ተሾመ ገመቹ ፣ ውይይቱ የጋራ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠና የሀገራችንን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚያስችል ሁኔታ በስኬት መካሄዱን ገልፀዋል።
አሜሪካና ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን በመከላከል ፣ በስልጠና ፣ በቴክኖሎጂ እና በወታደራዊ መረጃ መስኩ በጋራ ለመስራት በሚያስችል መልኩ መስማማታቸውን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ ፣ ለአፍሪካና ለቀጠናው ሰላም መረጋገጥም በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ጠቁመዋል።
የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የሰራዊታችንን ሁለንተናዊ አቅም ለማሻሻልና ለቀጠናው ሰላም የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official