ኮሩ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ፅንፈኛው መስርቶት የነበረውን ማከማቻ ደመሰሰ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም

በደቡብ ጎንደር ዞን በተለያዩ አካባቢዎች ፅንፈኛውን ቡድን እየደመሰሰ የሚገኘው ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ይመር ሀገር አፈርሳለሁ ብሎ የተነሳውን ፅንፈኛ ሀይል እያጠፋን እንገኛለን ብለዋል።

ፅንፈኛው ቤዝ መስርቶ የተለያዩ የሀገር ሀብትና ንብረት እየዘረፈ የሚያከማችበትና እራሱም የሚደበቅበት ቆማ በተባለው ስፍራ የሚገኘው ማዘዣው ሙሉ ለሙሉ ተደምስሷል ነው ያሉት።

እናት በምጥ ተይዛ ወደ ህክምና ማዕከል የምትወሰድበትን አምቡላንስ ሳይቀር ዘርፎ በመውሰድ ለዕኩይ አላማው መገልገያ ሲያደርግ እንደነበር የገለፁት አዛዡ አምቡላንሶችና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ከህብረተሰቡ ዘርፎ ያከማቸው 49 ኩንታል እህልና ሌሎች ንብረቶች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል።

ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ይመር ግዳጃችንን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ ወደ ልማት ስራው እንዲያተኩር ለማስቻል ዘመቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

ዘጋቢ ብርሃኑ አባተ

ፎቶግራፍ ከክፍሎች

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https:///channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ስፖርት

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ