ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።

በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ጉጂ ዞን በሰላም እና ፀጥታ ሥራ ላይ ለተሰማራው የመከላከያ ሠራዊት ምስጋና እና እውቅና ሰጥቷል።

የጉጂ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ብዙነህ፤ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች ምክንያት ሕዝብ እና የመንግሥት መዋቅር በሚፈለገው ደረጃ ለመንቀሳቀስ የሚቸገሩበት ሁኔታ እንደነበር አስታውሰዋል።

ይሁንና ዛሬ ላይ ሰላም በመስፈኑ ችግሩን እንደታሪክ ለማውራት እንድንበቃ ላደረጉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል።

ለሰላም ማስፈኑ ሥራ ውድ ሕይወታቸውን ሰጥተው ቀና ብለን እንድንሄድ ላደረጉን የመከላከያ ሠራዊት አባላት ምስጋና መስጠት የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ሲሉም ገልፀዋል።

እንደተቋም ለተከናወኑ የሰላምና ደኅንነት ጥበቃ ሥራዎች የጉጂ ሕዝብ እና አስተዳደር ለሰጠን ዕውቅና አክብሮታችን የላቀ ነው ያሉት የደቡብ ዕዝ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ግርማ አየለ ፤ የተሰጠን እውቅና የሠራዊቱን እና የሕዝባችንን ትሥሥር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ኢቢሲ እንደዘገበው ሠራዊቱ ከአካባቢው የፀጥታ አካላት እና ከማኅበረሰቡ ጋር በሠራቸው የፀጥታ ሥራዎች ተቀዛቅዞ የነበረው የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴ አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መነቃቃቱ ተገልጿል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።