የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 


የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በወታደራዊ ሳይንስ፣ በስነ-ምግባር፣ በትጋት እና በሃገር ፍቅር ጥግ ያሰለጠናቸውን የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖች በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሃብታሙ፤ ጀግንነት በጦር ሜዳ መዋጋት ብቻ ሳይሆን ለእውነት፣ ለፍትህና ለሰላም ጸንቶ መቆም፣ ህዝብን በቅንነት ማገልገልና ሀገርን መወደድ ጭምር መሆኑን በምረቃ መርሃ-ግብሩ አሥገንዝበዋል።

ተመራቂዎቹ የተቀበሉትን የወታደራዊ አመራር ማዕረግና እውቀት ተጠቅመው የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላምና ደህንነት በጽናት መጠበቅ እንደሚጠበቅባቸውም አሥገንዝበዋል።

ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሀብታሙ እንደገለጹት፤ ተመራቂዎቹ በቆይታቸው አካላዊ፣ አእምሯዊና ስነ-ልቦናዊ ፈተናዎችን አልፈው የላቀ የጦር አመራር ክህሎትን ተላብሰዋል።

ትምህርቱም በንድፈ-ሀሳብና በጠንካራ የመስክ ልምምዶች የተደገፈ በመሆኑ፣ አዲሶቹ መኮንኖች በማንኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ሀገራዊ ግዴታቸውን በብቃት የመወጣት ሙሉ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንዳላቸው አረጋግጠዋል።

አካዳሚው የተሰጠውን ሀገራዊና ተቋማዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት የዘመኑን የቴክኖሎጂና የእውቀት እድገት ያገናዘቡ የትምህርትና የስልጠና ማሻሻያዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል። 

በሳይንሳዊ ጥናቶች ላይ በመመስረት የካዴት ትምህርቱን ደረጃ ከማሳደግ ባለፈ፣ የከፍተኛ አመራሮችንና ባለሙያዎችን አቅም የሚያጎለብቱ የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞችን ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የአካዳሚው አዛዥ ጠቁመዋል።

ከዋናው የትምህርትና ስልጠና ተልዕኮ ጎን ለጎን፣ አካዳሚው የአካባቢውን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በግብርና፣ በእንስሳት እርባታና በራስ አቅም የመሰረተ-ልማት ግንባታ በርካታ የአካባቢ ልማት ስራዎችን በማከናወን ረገድ አርአያነት ያለው ሰፊ እንቅስቃሴ አድርጓል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሀብታሙ  ይህም ተቋሙ የወታደራዊ ትምህርት ማዕከል ብቻ ሳይሆን የማህበረሰብና የልማት አጋር መሆኑን ዳግም በተግባር ያረጋገጠበት እንደሆነ አብራርተዋል።

በመጨረሻም ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሃብታሙ ተመራቂዎች ላለፉት ሦስት ዓመታት የነበራቸውን የጽናትና የትጋት ጉዞ በማድነቅ ለመላው ተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘጋቢ አብርሃም ዘርጋው 
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።