የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።

የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽንና ዓለም አቀፉ የሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራትና በዘላቂ ጥቅም ላይ ያተኮረ የልማት ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረሙ።

በስምምነቱ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ማርታ ሉዊጂ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን፣ ስምምነቱ ለሀገራዊ ዕድገት፣ ለዘላቂ ልማትና ለሠራዊቱ ተጠቃሚነት የሚኖረው ሚና የጎላ መሆኑ ተገልጿል።

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ወይዘሮ ማርታ ሉዊጂ የሁለቱ ተቋማት ትብብር ከግንባታ ባለፈ ለሀገሪቱ የከተማ ልማት፣ ለሥራ ፈጠራና ለቴክኖሎጂ ሽግግር አዲስ ዕድሎችን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

በሳር ቤት አካባቢ የሚገነባው ዘመናዊ የመኖሪያና የከተማ ልማት ፕሮጀክት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ግንባታ በማስገንባት ለከተማዋ ዕድገትና ለኢኮኖሚው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር፣ የዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂና ዕውቀት ሽግግርን ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ተብሏል።

የሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ሰብሳቢ አቶ አሪፍ አልኩሪ በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ከመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ጋር በጋራ መስራት መጀመሩ የሚያስደስት እድል መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት አቅም ያላት ሀገር መሆኗን የጠቆሙት አቶ አሪፍ አልኩሪ ፣ ድርጅታቸው ያለውን ዓለም አቀፍ ልምድና የቴክኖሎጂ አቅም በመጠቀም ለሀገሪቱ ዕድገት የሚችለውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቁርጠኛ መሆኑን አስረድተዋል።

በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል የተባለው ፕሮጀክት የትብብር፣ የዘላቂ ልማትና የብልጽግና መሠረት ይሆናልም ብለዋል።

ሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ከ28 በላይ በሆኑ ሀገራት የተሰማራ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ስምንቱ በአፍሪካ የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል።

በዝግጅቱ ላይ በኢትዮጵያ የዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ አምባሳደር አቶ አብደላ ሀሰንን ጨምሮ ከፍተኛ የሰራዊቱና የድርጅቱ አመራሮች፣ ባለሀብቶችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ስፖርት

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።