ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት የእነኝህን ኃይሎች ፍላጎት እያከሸፈው ይገኛል ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ።

በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ካዴት ዕጩ መኮንኖች ምርቃት ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ቀጠና የምትገኘው ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶች በየዘመኑ ስትፈተን መቆየቷን አውስተው፤  በታሪካዊ ጣላቶች እና በባንዳዎች የተሰራው የክፍት ደባ ጉዳት አላደረሰም ባይባልም ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ይህን እኩይ የጥፋት ሴራ በጀግንነት እያከሸፈ ይገኛል ብለዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያም ፈተና ቢበዛባትም፤ ፈተናውን በጀግኖች ልጆቿ እያለፈች ትገኛለችም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ተመራቂዎችም ይህን አኩሪ ተጋድሎ ለማስቀጠል ለእናት ሃገራቸው በየዘመኑ መስዋዕትነት እየከፈሉ ይገኛሉ ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አካዳሚው ኢትዮጵያን ያስቀጠሉ ጀግኖች መኮንኖችን ያፈራ የወታደራዊ የልህቀት ማዕከል እንደሆነም አብራርተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አካዳሚው የስርዓተ ትምህርቱን ዘመኑ በሚጠይቀው እውቀት በማዘመን፣ በማሻሻል ለተቋማዊ ፕሮፌሽናሊዝም ምቹ መደላደል የፈጠረ አንጋፍ አካዳሚ ሥለመሆኑም ገልፀዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተመራቂ ዕጩ መኮንኖች ያሳዩትን ተነሳሽነት አድንቀው፤ በስልጠናው ያገኙት እውቀት የሚዳብረው በሚቀለቀሉበት የጦር ክፍል በተግባር በሚያገኙት ልምድ እና እውቀት ሥለሆነ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ዘጋቢ አብርሃም ዘርጋው
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።