ህገ-ወጥ የመሳሪያ አዘዋዋሪዎች ላይ የሚደረገው ከትትል ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ልዩ ስሙ አስጎሪ በተባለ ቦታ ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በስፍራው የተሰማራው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ክፍለጦር ባደረገው የተቀናጀ ክትትል ህገ ወጥ መሳሪያው በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፍቃዱ ጥላሁን ገልፀዋል፡፡

ክፍሉ በአካባቢው ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሽብር ቡድኖችን እየተከታተለ በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰላም ማስፈኑን ገልፀው የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተልዕኮ የሚጠቀምበትን የህገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር እና ንግድ ከምንጩ ለማድረቅ በአቅራቢዎችና በተቀባይ የጠላት ህዋሶች ላይ የሚደርገው ቁጥጥር የተሳካ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

ሰሞኑን በተደረገው ክትትል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችና ሽጉጥ፣ የብሬንና ልዩ ልዩ ተተኳሾች መያዛቸውንና ህገ-ወጥ መሳሪያ የሚገበያዩበትን ገንዘብ 15.600.00 (አስራ አምስት ሺ ስድስት መቶ ብር) መያዙን አስታውቀዋል፡፡

ኮሎኔል ፍቃዱ ለዚህ ኦፕሬሽን መሳካት ትብብር ያደረጉትን የአካባቢውን ማህበረሰብ አመስግነው የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የተለመደውን ትብብር ህዝቡ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ ዘገባው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

ወቅታዊ አጀንዳ

33
ኮሌጆች እና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የተቋሙን ዝግጁነት የሚያጠናክር ውጤታማ ስራዎችን ሠርተዋል።
32
ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል
31
ቆራጥና ግዳጁን በጀግነት የሚፈፅም መሪና ሠራዊት ማፍራት ተችሏል።     ሌተናል ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ
30
የውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን አቅም የሌላትና ደካማ ሀገር ለማድረግ ከመስራት አይቆጠቡም   ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
29
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በውጤት እየፈፀመ መሆኑ ተገለፀ።
28
ዕዙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ከምንጊዜውም በላይ በውጤታማነት እየተወጣ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

ስፖርት

33
ኮሌጆች እና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የተቋሙን ዝግጁነት የሚያጠናክር ውጤታማ ስራዎችን ሠርተዋል።
32
ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል
31
ቆራጥና ግዳጁን በጀግነት የሚፈፅም መሪና ሠራዊት ማፍራት ተችሏል።     ሌተናል ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ
30
የውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን አቅም የሌላትና ደካማ ሀገር ለማድረግ ከመስራት አይቆጠቡም   ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
29
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በውጤት እየፈፀመ መሆኑ ተገለፀ።
28
ዕዙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ከምንጊዜውም በላይ በውጤታማነት እየተወጣ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ