ህገ-ወጥ የመሳሪያ አዘዋዋሪዎች ላይ የሚደረገው ከትትል ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ልዩ ስሙ አስጎሪ በተባለ ቦታ ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በስፍራው የተሰማራው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ክፍለጦር ባደረገው የተቀናጀ ክትትል ህገ ወጥ መሳሪያው በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፍቃዱ ጥላሁን ገልፀዋል፡፡

ክፍሉ በአካባቢው ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሽብር ቡድኖችን እየተከታተለ በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰላም ማስፈኑን ገልፀው የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተልዕኮ የሚጠቀምበትን የህገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር እና ንግድ ከምንጩ ለማድረቅ በአቅራቢዎችና በተቀባይ የጠላት ህዋሶች ላይ የሚደርገው ቁጥጥር የተሳካ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

ሰሞኑን በተደረገው ክትትል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችና ሽጉጥ፣ የብሬንና ልዩ ልዩ ተተኳሾች መያዛቸውንና ህገ-ወጥ መሳሪያ የሚገበያዩበትን ገንዘብ 15.600.00 (አስራ አምስት ሺ ስድስት መቶ ብር) መያዙን አስታውቀዋል፡፡

ኮሎኔል ፍቃዱ ለዚህ ኦፕሬሽን መሳካት ትብብር ያደረጉትን የአካባቢውን ማህበረሰብ አመስግነው የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የተለመደውን ትብብር ህዝቡ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ ዘገባው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።