የሙስና ወንጀል ወስብስብ ዓለማቀፋዊ እና ሀገራዊ ስጋት መሆኑ ተገለፀ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

የሙስና ወንጀል በማንኛወም የስራ ዘርፍ ላይ ሊከሰት እና ሊያጋጥም የሚችል ወስብስብ ዓለማቀፋዊ እና ሀገራዊ ስጋት ያለው እና ለሀገር ዕድገት እንቅፋት የሆነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የመከላከያ ስነ-ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት “ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግደታየን እወጣለሁ” በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያ መከለከያ መረጃ የሠራዊት አባላት እና ሲቪል ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የመከላከያ ስነ-ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት የሙስና መረጃ ትንተና ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ሺሻይ ተስፋሁን ሙስና በየትኛውም የስራ መስክ ላይ በስውር እና በረቀቀ መንገድ ሊፈፀም የሚችል ወስብስብ ወንጀል በመሆኑ ዓለማቀፋዊ እና ሀገራዊ ስጋት እየሆነ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡

ወንጀሉን ውስብስብ ከሚያደርጉት ጉዳዮች አንዱ የሙስና ወንጀል ሲፈፀም ጉዳቱ በቀጥታ በአንድ ግለሰብ ወይም ቡድን ላይ አለማረፉ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የሁሉም የሆነ የማንም አይደለም በሚል የተሳሳተ ሀሳብ ወንጀሉን በጋራ ለመከላከል ቸልተኝነቱ እየበዛ በመምጣቱ ወንጀሉ እየተስፋፋ በዓለም ደረጃ አሁን ከደረሰበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል፡፡

የስልጠናው አስተባባሪ የኢትዮጵያ መከላከያ መረጃ ስልጠና ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ያሬድ ሰለሞን የሰራዊቱ ቁልፍ ተግባር የሀገርን ዳር-ድንበር በመጠበቅ የህዝቦቿን ሰላም በፅኑ መሰረት ላይ ማቆም ቢሆንም በየሚሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ባላማወቅ ለቀላልም ሆነ ለከባድ የሙስና ወንጀሎች ተጋላጭ እንዳይሆን ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው ሀገሩን በፍቅር የሚያገልግል እና በስነ-ምግባር የታነፀ ወታደር እንዲቀረፅ ሁሉም የተቋሙ አባል የራሱን ድርሻ እንዲወጣ በማደረግ በኩል የራሱን ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል፡፡

በብርሃን እንዳየሁ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ስፖርት

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ