ዕዙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ከምንጊዜውም በላይ በውጤታማነት እየተወጣ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የምዕራብ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በዕዙ ጠቅላይ መምሪያ የበጀት ዓመቱን እቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ማጠቃልያ ላይ የተገኙት የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት የውስጥም ሆነ የውጭ ፀረ-ሰላም ሃይሎችን በመደምሰስ አንፀባራቂ ድል ከማስመዝገብ የሚያግደን ሃይል አለመኖሩን በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን ብለዋል።

ሠራዊቱ እንደባለፉት ጊዜያቶች ሁሉ የተሰጠውን ትልቅ ሃገራዊ ግዳጅ ውጤታማ በሆነ መልኩ እየፈፀመ የሚገኝ መሆኑን ገልፀው ለተልዕኮው ቅድሚያ ሰጥቶ በመስራት የበለጠ ድል ማስመዝገብ የሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

ሠራዊታችን በተሰማራበት ቀጠና በሽብርተኝነት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሃገራችን የሰላም ማነቆ እየሆኑ ያሉ ፅንፈኛ ሃይሎችን ዳግም የህዝባችን ስጋት እንዳይሆኑ ለማድረግ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑንም ጄኔራል መኮንኑ ተናግረዋል፡፡

ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሠረት በቀጠናው የፅንፈኛውን እና የአሸባሪውን የሸኔ ቡድን በመደምሰስ ያሳካናቸውን ድሎች አቅበን የህዝባችንን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ መስራትና ከአካባቢው የመስተዳደር አካላት ፣ የፀጥታ ሃይሎች ፣ ከሃገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ጋር በመቀናጀት ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥና ዋስትና ሆኖ መቀጠላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ዕዙ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መሰረተ ድንጋይ ከተቀመጠበት ዕለት ጀምሮ እስከ ፍፃሜው ዋዜማ ድረስ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን መደረጉ የሠራዊታችንን ጥንካሬ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ከህዝባችን ጋር ያለንን የሰላም እና የልማት ትስስር ይበልጥ አጠናክረን በመቀጠል የኢትዮጵያን ሰላም እና አንድነት አስጠብቀን ማቆየት አለብንም ብለዋል።

ዘጋቢ ፍፁም ከተማ
ፎቶ ግራፍ ሽመልስ እሸቱ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
http://localhost/defensenew/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።