የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የወገብ ህመም በብዙ ምክንያቶች ይመጣል ለምሳሌ፡-
• የወገብ አጥንት መዛነፍ
• የመገጣጠሚያ አካባቢዎች መቆጣት
• የአጥንት መብቀል
• የተለያዩ ኢንፌክሽኖች (የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ፣ የማህፀን ኢንፌክሽን ሴቶች)
• አደጋ (መደብደብ፤ ምት ወዘተ)
• ከመጠን ያለፈ ውፍረት
• እግርን አጣምሮ መቀመጥ፡-የዳሌ ጡንቻ እንዲወጣጠር ስለሚያደርግ ህመም ይፈጥራል
• ለብዙ ሰዓት መቆም
• ሲጋራ ማጨስ፡- ሲጋራ በውስጡ ኒኮቲን ስላለው በቂ ሆነ ደም ዝውውር እንዳይዳረስ ስለሚያደርግ
የወገብ ህመም ሲፈጠር ወደ ሀኪም መሄድ የሚያስፈልጉ ጊዜዎች፡-
• የእግር መደንዘዝ ካለ ወይንም መስነፍ
• ሽንትና ሰገራ የመቆጣጠር ችግር ካለ
• ትኩሳት ካለ
• ከዚህ በፊት የአጥንት መሳሳት ወይንም ካንሰር ህመምተኛ ከሆኑ
• ህመሙ በጣም እየባሰ መሄድና በእረፍት ወይንም
• በአቀማመጥ የማይሻል ከሆነ
• ህመሙ በሳምንት ውስጥ ለውጥ ከሌለው የወገብ
• ህመም ሲፈጠር ቀላል የህመም ማስታገሻ በመውሰድ ማስታገስ ይቻላል፡፡
መፍትሄው
• በጊዜ ሂደት ህመሙ እየጠፋ እንደሚሄድ አይርሱ፡፡
• ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የእንቅሳቃሴ ህክምና (ፊዚዮቴራፒ) በማድረግ ማስተካከል ይቻላል፡፡
• ከዚህ ሌላ ደግሞ የካይሮፕራክቲክ ህክምና እንዲሁም አኮፓንቸር ህክምና ደግሞ ውጤታማ ናቸው፡፡
የወገብ ህመም እንዳይመለስ ምን ማድረግ ያስፈልጋል
• ምንም ጊዜ ቢሆን በህመም ላይም እንኳን እንቅስቃሴ ማድረግ ጥሩ ነው፡፡
• በተቻለዎት መጠን ይንቀሳቀሳሉ ምክንያቱም እንቅስቃሴ ባደረጉ ቁጥር የወገብ ህመም የመሻል እድሉ እየጨመረ ይሄዳል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ