ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ሴቶች ውጤታማ የስራ አፈፃፀም እንዲያስመዝገቡ ምን መሥራት ይገባል በሚል ርዕሠ ጉዳይ ከመከላከያ ልዩ ልዩ ስታፍ ክፍሎች ከተውጣጡ የሠራዊት አባላት እና ሲቪል ሴት ሰራተኞች ጋር ውይይት አድርጓል።

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ በርካታ የህይወት ውጣ ውረድን አልፈው በሲቪሉ ዓለምም ሆነ በውትድርናው ዓለም የውድድር መድረክ ላይ አልፈው በአመራርነት ደረጃ ላይ የሚገኙት ሴቶችን አርአያ በማድረግ እናንተም ወደ ከፍታው ለመምጣት መገስገስ ይኖርባችኋል ብለዋል።

ውጤት ለማምጣት በመተባበር እና በመደጋገፍ ሊሰራ እንደሚገባ እና በግል መስራት ብቻውን የትም ሊያደርስ እንደማይችል ተነስቷል። ውጤታማ ድጋፍ ሰጭ ሲኖር ጠካራ ግዳጅ መፈፀም የሚችል ሀይል ለማፍራት  እንደሚቻልም ከመድረኩ እና ከተሳታፊዎች ሀሳብ ተነስቷል። 

የበታቾቹን በዓላማ የሚመራ እንዲሆኑ ልምድ እና ተሞክሮውን እያካፈለ የሰለጠነውን ስልጠና ወደተግባር እየቀየረ ለራሱ እና ለተቋሙ እድገት የራሱን ሚና የሚጫወት አባል ማፍራት አስፈላጊ በመሆኑ በትውልድ ቅብብሎሽ ሂደት ውስጥ ለማለፍ ራስን ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

ለለበሱት ዩኒፎርም ተገዥ መሆን በወታደራዊ ዲሲፕሊን መመራት የእርስ በእርስ ግንኙነትን ማጠናከር  ለተሰማሩበት ሙያ የሚመጥን ልምድና ችሎታ ማካበት  እና ራስን በትምህርት ማሳደግ ውጤታማ የስራ አፈፃፀም ለማስመዝገብ አስፈላጊ ነገሮች መሆናቸው በውይይቱ በሰፊው ተነስቷል።

ዘጋቢ ብርሃን እንዳየሁ
ፎቶግራፍ ዕፀገነት ዴቢሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።