ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉ የመከላከያ የሠው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ ገለፁ።

የመከላከያ የሠው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ ከሁሉም የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎች የተወጣጡ የሠው ሃብት አመራር ባለሙያዎችን በሠው ሀብት አስተዳደር የሙያ ዘርፍ አሰልጥኖ አስመርቋል።

በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የመከላከያ የሠው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ የተገኙ ሲሆን በተካሔደው ስልጠና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ከሰጡ በኋላ

ባደረጉት ንግግር መከላከያ እንደተቋም በሁሉም መስክ ስኬታማ የግዳጅ አፈጻጸም እያስመዘገበ እንደሚገኝ አውስተዋል።

በመከላከያ የሠው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ በኩል  በሠው ሀብት አስተዳደር የሙያ ዘርፍ ለወራት የተሠጠው ስልጠናም ወትሮ ዝግጁነትን ወደ ላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር በኩል የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ አክለው ተመራቂዎቹ በስልጠና ቆይታቸው የጨበጡትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር የተቋሙን አሰራር እና ደንብ ማዕከል ባደረገ መልኩ ተልዕኳቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ ቢዝነስ እና ማህበራዊ ጥናቶች ኮሌጅ ዳይሬክተር ኮሎኔል መላኩ ደመላሽ  በበኩላቸው ሰልጣኞች በቆይታቸው  የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ስልጠና በመከታተል የተመደበላቸውን የትምህርት ክፍለ ጊዜ በመሸፈን በሠው ሀብት አስተዳደር የሙያ ዘርፍ ትልቅ አቅም መጨበጣቸውን

ገልፀዋል

በስልጠና ቆይታቸው ሊያሰራቸው የሚችል በቂ ክህሎት ሊያዳብሩ መቻላቸውን ከተመራቂዎቹ መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

ወንድማገኝ ታደሠ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማስታወቂያ

No Posts Found

ክንውን

1
2
3
4
5
previous arrow
next arrow

ወቅታዊ አጀንዳ

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ስፖርት

s
ሠላምን በማፅናት ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት  እየተሰራ ነው። ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ 
IMG_20250502_114207_631
ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር  ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
IMG_20250416_093208_823
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
j,shuma
አመራር በትንሽ ኪሳራ ትልቅ ድል ማስመዝገብ የሚችለው ራሱን በማብቃት ዘመናዊ ሠራዊት ሲገነባ ነው። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
IMG_20250409_161558_051
የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን
one
ስልጠና የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው  :-ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ