የአላጌ  ጀግኖች አምባና ማገገሚያ ማዕከልን የረጅም ታሪክ ማስቀጠል ተገቢ ነው።      ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም

የአላጌ  ጀግኖች አምባና ማገገሚያ ማዕከል ረጅም ታሪክ ያለው በመሆኑ በማዕከሉ የሚገኙ አበላት ታሪኩን በጀግንነት የማስቀጠል ሃላፊነት እንዳለባቸው ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ገልፀዋል።

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ  ይልማ በማዕከሉ በመገኘት አባላቱ የማዕከሉን ታሪክ ከማስቀጠል ባሻገር የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ ዝግጁነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አመላክተዋል።

ማዕከሉ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና አንድነትን ለመጠበቅ ሲሉ የአካል መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖችን የመንከባከብ ተልዕኮውን በአግባብ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀው ማዕከሉ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ለሠራዊቱ ሞራል ከመሆን በተጨማሪ ተስፋ እንደሚሆን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገርን የመበታተን እኩይ ዓለማቸውን ለማሳካት ሁሌም እንደማይተኙ የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ሠራዊቱ የጠላት ፍላጎትን ለማክሸፍ ዝግጁነቱን ማረገገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የአላጌ ጀግኖች አምባና ማገገሚያ ማዕከል በምግብ ራስን የመቻል ተግባር እውን ለማድረግ እያከናወነ ያለው የልማት ሥራ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል። ጀግኖችንም ጎብኝተዋል። ዘገባው የደስታ ተረፋ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።