የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም
በአትሚስ የሴክተር 3 ኢንስፔክሽን ኃላፊ አቶ ጀምስ ነካሻ የ2024 የመጀመሪውን ሩብ ዓመት የሰራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ በተደረገው ኢንስፔክሽን ሠላም አሥከባሪ ሻለቃው በጥሩ አቋም ላይ እንደሚገኝ አረጋግጧል።
ከጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመስራቴ ደስተኛ ነኝ ኢትዮጵያዊያን መዋጋት ጠላትን ማንበርከክና ማሽነፍ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በአትሚስ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ የተሳካ እንዲሆን ለሱማሊያ ህብረተሰብ መስዋዕትነት እየከፈሉ የሚገኙ ናቸው ሲሉ መሥክረዋል።
ሠራዊቱ ለተልዕኮ ስኬት ቅድሚያ በመስጠት ንብረቶቹ ደህንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን የረጃም ጊዜ እንክብካቤና ጥንቃቄ እንደሚያደርግ ማሳያ ነው ተልዕኮውን ለመወጣት የሚረዳውን ንብረቶች በመንከባከብም አርአያ ነው ብለዋል።
የሴክተር 3 ሰላም ማስከበር ኢንስፔክሽን ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ግርማ ሽብሩ ሁሉም የሴክተሩ አባላት በተሰማሩበት በባይድዋ፣ በቡራካባ፣ በባርደሬ፣ በገብርሃሬ፣ በዲንሱር፣ በባርደሌ፣ በቡርዱቦና በቀንሳ ሃደሬ አካባቢዎች የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ሻለቃ ዝግጁነት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።
የሴክተር 3 ጥገና ኃላፊ ሻምበል መንግስቱ ማቲዎስ በክፍላችን የሚገኙት ሞያተኞች ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እንደ ወታደር የአትሚስን አህጉራዊ ተልዕኮ ለመፈፀም መንግስትና ህዝብ የሰጠንን አደራ እየተወጣን የተበላሹ ተሸከርካሪዎችንና ማሽነሪዎችን በመጠገን ለማንኛውም ግዳጅ ዝግጁ ነን ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ ሠመረ እሸቱ
ፎቶግራፍ ከሻለቆች