የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም
በደቡብ ጎንደር ዞን በተለያዩ አካባቢዎች ፅንፈኛውን ቡድን እየደመሰሰ የሚገኘው ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ይመር ሀገር አፈርሳለሁ ብሎ የተነሳውን ፅንፈኛ ሀይል እያጠፋን እንገኛለን ብለዋል።
ፅንፈኛው ቤዝ መስርቶ የተለያዩ የሀገር ሀብትና ንብረት እየዘረፈ የሚያከማችበትና እራሱም የሚደበቅበት ቆማ በተባለው ስፍራ የሚገኘው ማዘዣው ሙሉ ለሙሉ ተደምስሷል ነው ያሉት።
እናት በምጥ ተይዛ ወደ ህክምና ማዕከል የምትወሰድበትን አምቡላንስ ሳይቀር ዘርፎ በመውሰድ ለዕኩይ አላማው መገልገያ ሲያደርግ እንደነበር የገለፁት አዛዡ አምቡላንሶችና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ከህብረተሰቡ ዘርፎ ያከማቸው 49 ኩንታል እህልና ሌሎች ንብረቶች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል።
ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ይመር ግዳጃችንን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ ወደ ልማት ስራው እንዲያተኩር ለማስቻል ዘመቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
ዘጋቢ ብርሃኑ አባተ
ፎቶግራፍ ከክፍሎች
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https:///channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official