ለምረቃ የበቁ የመሠረታዊ ኮማንዶ ሰልጣኝ አባላቱ የቁርጠኝነት ማሳያ ስለመሆናቸው ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም.

የልዩ ዘመቻዎች ማሰልጠኛ ማዕከል መሠረታዊ ኮማንዶዎችን አሰልጥኖ ለ43 ጊዜ አስመርቋል።

ካራማራ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የመሠረታዊ ኮማንዶ ሰልጣኝ አባላቱ የተለያዩ ወታደራዊ ትርኢቶችን በማሳየት ብቃታቸውንም አረጋግጠዋል።

የ43ኛው ዙር የኮማንዶ ሰልጣኞች ምረቃ ስነስርዓት የሰልጣኞቹ ጥንካሬና ብቃት ጎልቶ መታየቱን የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል።

ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ሰልጣኞቹ የሚሰጣቸውን ማንኛውንም ውስብስብ ግዳጅ እንኳን ቢሆን ሊዋጡ የሚችሉ የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የልዩ ሀይል አባላት ማፍራታቸውን ተናግረዋል።

አዛዡ አክለውም ማሰልጠኛው የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉን የሚያጠናክሩ ለቀጣይም ሀገራዊ ተልዕኮ ዝግጁ የሆኑ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል የማጠናከርና የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ተመራቂ አባላቱ የቀይ መለዮ አለባበስ ስነ ስርዓቱም በጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የለበሱ ሲሆን ሀገራቸውን በቅንነት ለማገልገል ያላቸውን ቁርጠኝነት በቃለ-መሀላ አረጋግጠዋል።

በራሔል ገዛኸኝ

ወቅታዊ አጀንዳ

33
ኮሌጆች እና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የተቋሙን ዝግጁነት የሚያጠናክር ውጤታማ ስራዎችን ሠርተዋል።
32
ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል
31
ቆራጥና ግዳጁን በጀግነት የሚፈፅም መሪና ሠራዊት ማፍራት ተችሏል።     ሌተናል ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ
30
የውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን አቅም የሌላትና ደካማ ሀገር ለማድረግ ከመስራት አይቆጠቡም   ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
29
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በውጤት እየፈፀመ መሆኑ ተገለፀ።
28
ዕዙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ከምንጊዜውም በላይ በውጤታማነት እየተወጣ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

ስፖርት

33
ኮሌጆች እና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የተቋሙን ዝግጁነት የሚያጠናክር ውጤታማ ስራዎችን ሠርተዋል።
32
ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል
31
ቆራጥና ግዳጁን በጀግነት የሚፈፅም መሪና ሠራዊት ማፍራት ተችሏል።     ሌተናል ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ
30
የውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን አቅም የሌላትና ደካማ ሀገር ለማድረግ ከመስራት አይቆጠቡም   ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
29
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በውጤት እየፈፀመ መሆኑ ተገለፀ።
28
ዕዙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ከምንጊዜውም በላይ በውጤታማነት እየተወጣ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ