የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ሞዴል የሆነ ዩኒቨርሲቲ ነው   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የወታደራዊ ቴክኖሎጅ አቅምን በማሳደግ ረገድ ጠንካራ የምርምርና የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው የሠራዊታችንን ወታደራዊ የቴክኖሎጅ አቅም በማሣደግም ሆነ የልማትና ምርምር ማዕከል በመሆን በርካታ በራስ አቅም የተሠሩ ሥራዎችን እያከናወነ ነው። ዛሬ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላና ከፍተኛ የሠራዊቱ አመራሮች ይህንኑ ሥራ ተመልክተዋል።

ዩኒቨርሲቲው ሳይንሳዊ በሆነ አግባብ እየሰራቸው የሚገኙ ተሰፋ ሰጪ የምርምርና የልማት ተግባራት በቀጣይነት የመከላከያን ወታደራዊ አቅም የበለጠ ማሳደግ የሚችሉ ዩኒቨርሲቲዉ በሀገራችን በዚሁ ዘርፍ ሞዴል መሆኑን የሚያረጋግጡ የከፍታ ማሳያ ሥራዎች መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ አረጋግጠዋል።

ዘመኑ የቴክኖሎጂ እሽቅድድም የሚሥተዋልበት እንደመሆኑ መጠን ኢትዮጵያ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር ራሷን ማላመድ የምትችልበትን ጥበብ መፍጠር እንደሚገባ ያመላከቱት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩኒቨርሲቲው የታዩ የተጀመሩ የምርምርና የልማት ሥራዎችን ለማሣደግ ተቋሙ አሥፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ያደርጋል ብለዋል።

በሠው ሃይል ግንባታ በኩል ሀገሩን የሚወድ የሠለጠነ ዩኒቨርሲቲውን የሚወክል ሀይል መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ የጠቆሙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ለተቋሙ የከፍታ ጉዞ ለሚተጉ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ብርጋዲየር ጄኔራል ከበደ ረጋሳና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አመሥግነዋል።

በመማር ማሥተማር ሂደቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሠውና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ስራው በርካታ ተግባራትን እያከናወነ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ አሥራ ሦስት የምርምርና ልማት ሥራዎችን ሥለማጠናቀቁና አሥራ አንዱ ደግሞ በሥራ ሂደት ላይ ሥለመሆናቸው ተገልጿል።

ዘጋቢ ውብሸት ቸኮል

ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

http://localhost/defensenew

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

photo_2025-10-08_21-49-49
ከጀግኖች አባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር በጀግንነት ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
photo_2025-10-08_16-00-00
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ ነው።   አቶ ጌታቸው ኃይለማርያም
photo_2025-10-08_21-36-23
የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -   ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
photo_2025-10-06_09-06-37
ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።
photo_2025-09-23_22-13-45
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አቅም እየገነባ ይገኛል።     ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
photo_2025-09-23_17-24-05
ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

ስፖርት

photo_2025-10-08_21-49-49
ከጀግኖች አባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር በጀግንነት ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
photo_2025-10-08_16-00-00
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ ነው።   አቶ ጌታቸው ኃይለማርያም
photo_2025-10-08_21-36-23
የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -   ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
photo_2025-10-06_09-06-37
ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።
photo_2025-09-23_22-13-45
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አቅም እየገነባ ይገኛል።     ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
photo_2025-09-23_17-24-05
ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ