ለጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መረጃ እና ማገገሚያ ማዕከል ድጋፍ ተደረገ።

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት  በየደረጃው የሚገኙ የተቋሙን ክፍሎች በማስተባበር በበጀት ዓመቱ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል። በዛሬው ዕለትም ከ240 በላይ ለሚሆኑ የጌርጌሴኖን ሴት የአእምሮ ህሙማን ከዋና መምሪያዎች እና ሌሎች ክፍሎች ጋር በመተባበር ድጋፍ ተደርጓል። 

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ሠራዊቱ አቅሙ በፈቀደ መጠን ከኪሱ በማዋጣት ከ348 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የአልባሳት እና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ለሀገር ዋጋ የከፈሉ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ራሳቸውን መርዳት የተሳናቸውን ወገኖቻችንን መርዳት እና ማገዝ የሁላችንም ሀላፊነት ሊሆን ይገባል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ሌላው የማህበረሰብ ክፍልም መጥቶ ሊጎበኛቸው እና ድጋፍ ሊያደርግላቸው እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

እኛ በውትድርና ሙያችን ለሀገርና ለህዝብ ከምንከፍለው እንዲሁም ከምንሰራው የሙያ መስክ እና ከምንሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ካለን ላይ ቀንሰን ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረጋችን ለሌላውም አርአያ መሆን አለብን ያሉት የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልና ዲያግኖስቲክ ማዕከል ሃላፊ ብርጋዲየር ጄኔራል ሽዋዬ ሃይሌ ናቸው።

የማዕከሉ መስራች ሊቀ-ህሩያን መለሰ አየለ ለተደረገው ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቅርበው ለሀገር መስዋዕትነት የምትከፍሉ የሀገር ምሰሶዎች መጥታችሁ ስለጎበኛችሁን እጅግ ደስ ብሎናል እናመሠግናለን ብለዋል።

ማዕከሉ በ1998 ዓ.ም በበጎ ፈቃደኞች መመስረቱን ገልፀው ጎዳና ላይ የወደቁትን በማንሳት ወደ ቀደመ ጤንነታቸው ለመመለስ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ብዙዎቹ ከጎዳና ላይ የተነሱት ህሙማን በአሁኑ ሰዓት ከህመማቸው አገግመው ለሌሎቹ አገልግሎት እየሰጡ በማየታቸው ከመቼውም ጊዜ በላይ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል

ዘጋቢ ብርሃን እንዳየሁ

ፎቶ ግራፍ ዕፀገነት ዴቢሳ

ወቅታዊ አጀንዳ

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ስፖርት

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ