ምዕራብ ዕዝ ተልዕኮን በድል ለመወጣት የሚያሥችል ስልጠና እየሠጠ መሆኑ ተገለፀ።

ዕዙ በሚታወቅበት ጀግንነት ለማስቀጠል በቀጣይ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በድል ለመወጣት ሁለገብ ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሜጄር ጄኔራል ሙላት ጀልዱ ተናግረዋል።

ጄኔራል መኮንኑ በምዕራብ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ዴዴሳ ተገኝተው ከኮሮች የተወጣጡ የሬጅመንት አመራሮች እና የሻምበል አመራሮች እንዲሁም የቡድን መሳሪያ ሰልጣኞች የስልጠና ማጠቃለያ ትምህርት ሰጥተዋል።

የሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስና የመካከለኛ አመራሩን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ለአመራሩ የሚሰጠው ሁለገብ ስልጠና አስተዋፅኦው ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ሜጄር ጄኔራል ሙላት ጀልዱ በዕውቀት የዳበረ በክህሎት የላቀና በአስተሳሰብ የበለፀገ ተተኪ ለማፍራት ያላሰለሰ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

አመራሩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ላይ ያለውን እውቀት በማጎልበት እንዲሁም ስልታዊ ቴክኒካዊና ታክቲካዊ ግንዛቤውን በማሳደግ አባላቱን በእውቀት ላይ ተመስርቶ በመምራት ፈጣንና ተነቃናቂ አሃድ ፈጥሮ በተልዕኮዎቹ ሁሉ ድንገተኝነትን ለማትረፍ የሚያስችለውን አስተማማኝ አቅም ስልጠናው ፈጥሮለታል ሲሉ ጀኔራል መኮንኑ ተናግረዋል።

ሜጄር ጄኔራል ሙላት ጀልዱ ሠራዊቱን በማያቋርጥ ስልጠና መገንባት የሞራል ተነሳሽነቱን ማሳደግና በጠላቶቹ ላይ የበለጠ እልህና ቁጭት ፈጥሮ ወኔና ጀግንነትን በመላበስ ስምሪቶቹን በመረጃ ላይ ተደግፎና አዳዲስ ስልታዊ እንቅስቃሴዎችን ተጠቅሞ በማካሄድ በአጠረ ጊዜና ባነሰ ኪሳራ ድል የሚቀዳጅበትን አቅም ከስልጠናው አግኝቷል ብለዋል ።

የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የዕዙ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮሎኔል ጀንበሬ ማሞ በበኩላቸው የስልጠናው ዓላማ በክህሎትና በዲስፕሊን የታነፀ የሬጅመንት እና የሻምበል አመራር  እንዲሁም ብቁ የቡድን መሳሪያ ምድብተኞችን መፍጠር መሆኑን ጠቁመው ስልጠናው አመርቂ ከመሆኑም በላይ  የአመራሩ ድጋፍ የታከለበት በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል።

ዘጋቢ ፍፁም ከተማ
ፎቶግራፍ አከለ አባተ

ወቅታዊ አጀንዳ

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ስፖርት

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ