የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አቅም እየገነባ ይገኛል።     ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ


የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ አመታዊ የስራ እንቅስቃሴዎቹን አስመልክቶ የማጠቃለያ መርሃ ግብር አከናወነ።

ዋና መምሪያው በአመቱ በተለያዩ የተቋሙ ክፍሎች ያከናወናቸውን የመሠረተ ልማት ግንባታ ስራዎች በፎቶ አውደ ርዕይ መልኩ አስጎብኝቷል።

በመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ዋና መምሪያው የተቋሙ ሪፎርም ዋና አካል ስለመሆኑ ተናግረዋል።

የመሃንዲስ ዋና መምሪያ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ዋና መሠረት ስለመሆኑም አንስተዋል።

ሰራዊታችን ለታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ከባድ የህይወት መስዋዕትነት በመክፈል የጠላትን ሴራ በማክሸፍ የሀገራችንን ትንሳኤ ስለ ማብሰሩ ገልፀዋል።

በቀጣይም ለሀገራችን እድገት በታላቅ የዝግጁነት መንፈስና ቁርጠኝነት የበለጠ ታሪክ ለመስራት  ሰራዊታችን ዝግጁ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የመሃንዲስ ዋና መምሪያው ያሉትን ጥንካሬዎች በማቀብ ለቀጣይ የተቋሙን የፕሮፌሽናል የግንባታ ሂደት የማጠናከር ተግባሩን በቆራጥነት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ዋና መምሪያው በአመቱ ለተከናወኑ አመርቂ ውጤቶች አብላጫ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ክፍሎች እና አባላቱ የሽልማትና እውቅና መርሃ ግብር አከናውኗል።

ዘጋቢ ራሔል ገዛኸኝ
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ስፖርት

mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።
F
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
A1
አንድ ሆነን በአድዋ እንዳስመዘገበነው ድል በጋራ ሆነን የአክሲዮን ማህበራችንን ስኬት እናረጋግጥ፦    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
P
በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ