ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።

በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ጉጂ ዞን በሰላም እና ፀጥታ ሥራ ላይ ለተሰማራው የመከላከያ ሠራዊት ምስጋና እና እውቅና ሰጥቷል።

የጉጂ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ብዙነህ፤ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች ምክንያት ሕዝብ እና የመንግሥት መዋቅር በሚፈለገው ደረጃ ለመንቀሳቀስ የሚቸገሩበት ሁኔታ እንደነበር አስታውሰዋል።

ይሁንና ዛሬ ላይ ሰላም በመስፈኑ ችግሩን እንደታሪክ ለማውራት እንድንበቃ ላደረጉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል።

ለሰላም ማስፈኑ ሥራ ውድ ሕይወታቸውን ሰጥተው ቀና ብለን እንድንሄድ ላደረጉን የመከላከያ ሠራዊት አባላት ምስጋና መስጠት የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ሲሉም ገልፀዋል።

እንደተቋም ለተከናወኑ የሰላምና ደኅንነት ጥበቃ ሥራዎች የጉጂ ሕዝብ እና አስተዳደር ለሰጠን ዕውቅና አክብሮታችን የላቀ ነው ያሉት የደቡብ ዕዝ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ግርማ አየለ ፤ የተሰጠን እውቅና የሠራዊቱን እና የሕዝባችንን ትሥሥር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ኢቢሲ እንደዘገበው ሠራዊቱ ከአካባቢው የፀጥታ አካላት እና ከማኅበረሰቡ ጋር በሠራቸው የፀጥታ ሥራዎች ተቀዛቅዞ የነበረው የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴ አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መነቃቃቱ ተገልጿል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

photo_2025-10-08_21-49-49
ከጀግኖች አባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር በጀግንነት ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
photo_2025-10-08_16-00-00
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ ነው።   አቶ ጌታቸው ኃይለማርያም
photo_2025-10-08_21-36-23
የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -   ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
photo_2025-10-06_09-06-37
ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።
photo_2025-09-23_22-13-45
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አቅም እየገነባ ይገኛል።     ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
photo_2025-09-23_17-24-05
ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

ስፖርት

photo_2025-10-08_21-49-49
ከጀግኖች አባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር በጀግንነት ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
photo_2025-10-08_16-00-00
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ ነው።   አቶ ጌታቸው ኃይለማርያም
photo_2025-10-08_21-36-23
የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -   ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
photo_2025-10-06_09-06-37
ለምስራቅ ጉጂ ዞን ሠላም አሥተዋፅኦ ላበረከተው ኮር ዞኑ ምስጋና አቀረበ።
photo_2025-09-23_22-13-45
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አቅም እየገነባ ይገኛል።     ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
photo_2025-09-23_17-24-05
ሴቶች በሁሉም መስክ ፊት በመሠለፍ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ተገለፀ።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ