ከጀግኖች አባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር በጀግንነት እናስቀጥላለን ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጄር ጄኔራል ዋኘው አለሜ ተናግረዋል።
ሜጄር ጄኔራል ዋኘው አለሜ በዕዙ ማሰልጠኛ ማዕከል ተገኘተው ስልጠና ላይ ከሚገኙ የሠራዊት አባላት ጋር በነበራቸው ቆይታ አባቶቻችን የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበርና የህዝቦቿን ደህንነት ለማስጠበቅ ለቅኝ ገዢዎች ሳይንበረከኩ በጀግንነት ተፋልመው ያስረከቡንን ሀገር ማስቀጠልና ለሰንደቋ በመዋደቅ ሠላምን ማረጋገጥ ከዚህ ትውልድ የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል።
ሜጄር ጄኔራል ዋኘው አለሜ ጠላቶቻችን ሀገራችንን ለማፍረስ የሚፈፅሙብንን ጥቃት ለመመከትና አገራችን እንዳትደፈር ራሳችንን በስልጠና ማብቃትና ማዘጋጀት እንዲሁም የወጊያ አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የሀገራችንን ሠላም ለማረጋገጥና የዕድገት ጉዞዋን ለማስቀጠል የምንከፍለው መስዋዕትነት በታሪክ የሚታወስ ነው ያሉት ሜጄር ጄኔራል ዋኘው አለሜ በቀጣይም በጀግንነት፣በዓላማ ፅናትና በቁርጠኝነት የኢትዮጵያን ከፍታ ማስቀጠል ይጠበቅባችኋል ሲሉ ለሠልጣኞች አሥገንዝበዋል።
ዘጋቢ ይሁን አሻግሬ
ፎቶግራፍ እያሱ ጃርሶ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official