በ2012 ዓ.ም እንደገና ወደ ስራ እንዲመለስ የተደረገው እና በአዲስ መልክ የተደራጀው የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለሀገር በሚያበረክታቸው ወታደራዊና ኮሜርሻል ምርቶቹ አማካኝነት በ2017 ዓ.ም ከኮርፖሬሽን ወደ ግሩፕ ያደገ የሀገር ሀብት ነው።
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ በአዲስ አመራር ተደራጅቶ ወደ ምርት እንዲገባ ከተደረገ በኋላ ወደ ትርፋማነት ተሸጋግሯል። እየተመዘገበ ያለውን ለውጥም በጥናት እና ምርምር አስደግፎ መቀጠል ችሏል።
በትናንትናው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) በተገኙበት ሰባተኛው ታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና ሥነሥርዓት ላይም ኢንዱስትሪ ግሩፑ አንዱ ለመሆን በቅቷል።
በዚሁ ሀገራዊ የዕውቅና እና የምስጋና መድረክ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ መከላከያ እያደረገ ያለውን ሪፎርም ተከትሎ ከኪሳራ ወደ ትርፋማ በመሸጋገር በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶክተር) የታማኝ ግብር ከፋይ የወርቅ ሽልማት ተበርክቶለታል።

ይህም ውጤት የመከላከያ ሪፎርም ስለመሳካቱ አንዱ አመላካችና ግሩፑም መንግስትና ሀገር በሚፈልገው መንገድ ላይ መሆኑን ያመላክታል።
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ አቶ ጌታቸው ኃይለማርያም ለመላው የኢንዱስትሪ ግሩፑ አመራር እና ሠራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ የተበረከተው ሽልማት የሁሉንም አመራር እና ሠራተኛ ሞራል እና ተነሳሽነት የሚያሣድግ ነው ብለዋል።
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ዋና ሥራ አሥፈፃሚው በቀጣይም ወታደራዊ እና ስቪል ምርቶችን ዘመናዊነትን በተከተለ አግባብ እንደሚያሥቀጥል ተናግረዋል። ዘገባው የመስከረም ብርሃኔ ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official