የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም
የአላጌ ጀግኖች አምባና ማገገሚያ ማዕከል ረጅም ታሪክ ያለው በመሆኑ በማዕከሉ የሚገኙ አበላት ታሪኩን በጀግንነት የማስቀጠል ሃላፊነት እንዳለባቸው ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ገልፀዋል።
የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ በማዕከሉ በመገኘት አባላቱ የማዕከሉን ታሪክ ከማስቀጠል ባሻገር የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ ዝግጁነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አመላክተዋል።
ማዕከሉ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና አንድነትን ለመጠበቅ ሲሉ የአካል መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖችን የመንከባከብ ተልዕኮውን በአግባብ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀው ማዕከሉ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ለሠራዊቱ ሞራል ከመሆን በተጨማሪ ተስፋ እንደሚሆን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገርን የመበታተን እኩይ ዓለማቸውን ለማሳካት ሁሌም እንደማይተኙ የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ሠራዊቱ የጠላት ፍላጎትን ለማክሸፍ ዝግጁነቱን ማረገገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአላጌ ጀግኖች አምባና ማገገሚያ ማዕከል በምግብ ራስን የመቻል ተግባር እውን ለማድረግ እያከናወነ ያለው የልማት ሥራ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል። ጀግኖችንም ጎብኝተዋል። ዘገባው የደስታ ተረፋ ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official