ማሰልጠኛ ማዕከሉ አሥተማማኝ የኮማንዶ ሃይል አሠልጥኖ እያበቃ ነው     ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ብላቴ በመገኘት የ4ኛ ዙር መሠረታዊ  ውትድርና ስልጠናን በማስጀመር የ44ኛ ዙር የኮማንዶ ሰልጣኞችን ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል።

ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ በዲስፕሊን የታነፀ ትክክለኛ ፅናትን የተላበሰ አገራዊ ፍቅር ያለዉ ኢትዮጵያዊ ሰራዊት የሚገነባበት እና ሰልጥኖ የሚወጣበት ትልቅ ማሰልጠኛ ማዕከል መሆኑን የገለፁት ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ እናንተም የአሰልጣኞችን የካበተ አቅም በመጠቀም በዲስፕሊን የታነፀ ጠንካራ እና አገራዊ ፍቅርን የተላበሰ ወታደር እና ኮማንዶ ለመሆን ጠንክራቹህ መስራት ይጠበቅባችኋል ብለዋል።

ኮማንዶ ማለት በታማኝነት እና በቅንነት ራሱን አሳልፎ በመስጠት ለአገሩም ለህዝቡም አኩሪ ታሪክ የሚሰራ የዉጊያ ማርሽ ቀያሪ የተበላሸ ዉጊያን በአጭር ሰዓት በመድረስ ዉጊያ የሚያስተካክል የዘገዩ ዉጊያዎችን የሚያፋጥን ጀግና ነዉ ፤ እናንተም የዚህ ክፍል አባል ለመሆን ፈቅዳችሁ መምጣታችሁ ደስ ያሠኛልና ጠንክራችሁ ሠልጥኑጨሲሉ አበረታትተዋል።

አገራችን ወደ ከፍታ እየተጓዘች ነዉ ለዚህ እድገት እና ከፍታ ደግሞ የሰራዊታችን ሚና የጎላ ነዉ ያሉት አዛዡ  እንደ ሃገር በተሰሩ የልማት ስራዎች ከኪሱ ገንዘብ አዉጥቶ ቦንድ ከመቁረጥ ጀምሮ በጉልበቱ እስከ መስራት እንዲሁም የሚሰሩ አገራዊ ልማቶች ደህንነታቸዉ ተጠብቆ እንዲጠናቀቁ እስከ ህይወት መስዋዕትነት የደረሰ አበርክቶ ማድረጉንም አንስተዋል።

በተቋሙ ዉስጥ የሙያ ባለቤት የሚያደርጉ እድሎች  መኖራቸዉን የገለፁት ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ ዉትድርና ሲነሳ ጦርነትን ብቻ ማሰብ ስህተት ነዉ ስለዚህ ራሳችሁን በማብቃት እና በማሳደግ የሙያ ባለቤት ሆናችሁ ለትዉልድ የሚሻገር ተግባርን በማከናወን አገራችሁንና ራሳችሁን የሚለዉጥ ይጠበቅባችኋል በማለት አስገንዝበዋል።

ዘጋቢ ምህረት ስመኝ
ፎቶ ግራፍ አብዱራማን ሃሰን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

16
ሰላም ፣ ልማትና የባህር በር ባለቤትነታችንን እናረጋግጣለን!!    ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 
13
ዛሬ ኩሩ ሀገርን ለሚጠብቅ ኩሩ ኃይል የሚገባውን ክብር የምንሰጥበት ታላቅ ቀን ነው    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
10
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።     ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ
9
የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
7
ከሃገር ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ሰላምን ለማፅናት በቁርጠኝነት እየሰራ ያለ የማይበገር የድል ሰራዊት።
4
መከላከያ ሠራዊት ሀገሩን በመስዋዕትነት ያፀና የሀገር ዘብ ነው።

ስፖርት

16
ሰላም ፣ ልማትና የባህር በር ባለቤትነታችንን እናረጋግጣለን!!    ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 
13
ዛሬ ኩሩ ሀገርን ለሚጠብቅ ኩሩ ኃይል የሚገባውን ክብር የምንሰጥበት ታላቅ ቀን ነው    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
10
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።     ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ
9
የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
7
ከሃገር ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ሰላምን ለማፅናት በቁርጠኝነት እየሰራ ያለ የማይበገር የድል ሰራዊት።
4
መከላከያ ሠራዊት ሀገሩን በመስዋዕትነት ያፀና የሀገር ዘብ ነው።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ