የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር መከላከል በግዳጅ አፈፃፀማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ክፍሎች እና አባላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅና ከማንኛውም ጥቃት የሚከላከል አስተማማኝ አየር መከላከል መገንባቱን አስታውቀዋል።

ታላቁ የህዳሴ ግድባችን በስኬት እንዲጠናቀቅ የምክትሉ አባላት የአየር ክልላችንን በጀግንነት በመጠበቅ ሃገርና ህዝብን ያኮራ ገድል ፈፅማችኋል በዚህም ልትኮሩ ይገባል ብለዋል።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር መከላከል
ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ባጫ በበኩላቸው ምክትሉ የሙያተኛውን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ እና የአየር መከላከል ትጥቆችንም ዘመኑን የዋጁ በማድረግ በኩል ሰፊ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረው በቀጣይነትም የሚሰጠንን ማንኛውንም ግዳጅ ለመወጣት በከፍተኛ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንገኛለን ነው ያሉት።

በመርሃ ግብሩ ለምክትሉ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱና ግዳጃቸውን በብቃት ለተወጡ ክፍሎች አባላትና አጋር አካላት የእውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

ዘጋቢ ይታያል ምህረት
ፎቶግራፍ ባጫ ለገሰ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

16
ሰላም ፣ ልማትና የባህር በር ባለቤትነታችንን እናረጋግጣለን!!    ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 
13
ዛሬ ኩሩ ሀገርን ለሚጠብቅ ኩሩ ኃይል የሚገባውን ክብር የምንሰጥበት ታላቅ ቀን ነው    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
10
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።     ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ
9
የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
7
ከሃገር ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ሰላምን ለማፅናት በቁርጠኝነት እየሰራ ያለ የማይበገር የድል ሰራዊት።
4
መከላከያ ሠራዊት ሀገሩን በመስዋዕትነት ያፀና የሀገር ዘብ ነው።

ስፖርት

16
ሰላም ፣ ልማትና የባህር በር ባለቤትነታችንን እናረጋግጣለን!!    ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ 
13
ዛሬ ኩሩ ሀገርን ለሚጠብቅ ኩሩ ኃይል የሚገባውን ክብር የምንሰጥበት ታላቅ ቀን ነው    ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
10
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።     ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ
9
የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
7
ከሃገር ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ሰላምን ለማፅናት በቁርጠኝነት እየሰራ ያለ የማይበገር የድል ሰራዊት።
4
መከላከያ ሠራዊት ሀገሩን በመስዋዕትነት ያፀና የሀገር ዘብ ነው።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ